ሃሰኩራ ጹነናጋ

ከውክፔዲያ


በ1607 በሮማ ሲጎበኙ የተድረገው የሃሰኩራ ስእል

ሃሰኩራ ሮኩኤሞን ጹነናጋ (支倉六右衛門常長, 15631614 ዓ.ም.) ጃፓናዊ ሳሙራይ (መኮንን) እና የሰንዳይ ዳይምዮ (ገዥ) የዳተ ማሳሙነ ሎሌ ነበሩ። ከ1605 ዓ.ም. እስከ 1612 ዓ.ም. ድረስ ወደ ሜክሲኮእስፓንያፈረንሳይ እና ጣልያን አገሮች አምባሳደር ሆነው ይፋዊ ጉብኝት አደረጉ። ከማንም በፊት ወደ አሜሪካ አህጉር የተላኩት የጃፓን መንግሥት ልዩ ተወካይ እሳቸው ነበሩ። ከዚያ በላይ የርሳቸው ተልዕኮ በታሪክ መዝገብ የሚታወቀው መጀመርያው ጃፓናዊ-ፈረንሳያዊ ግንኙነት ሆኗል።

ስለ ልጅነታቸው ብዙ ባይታወቅም፣ በታይኮ (እንደራሴ) ሂደዮሺኮርያ ላይ በተደረገው ወረራ ጊዜ በ1584 እና በ1589 ዓ.ም. ዘመቻዎች ልምድ ያለው ሳሙራይ ሆነው እንደ ተሳተፉ ይታወቃል።

16ኛው ምዕተ ዓመት ከተካሄደው አንድሬስ ዴ ኡርዳኔታ ጉዞ ጀምረው እስፓንያውያንፊሊፒንስ የያዙትን መሬት መሠረት አድርገው በሜክሲኮና በቻይና መካከል ፓሲፊክ ውቅያኖስን ይሻገሩ ነበር። በ1563 ዓ.ም. ማኒላ ለምሥራቅ እስያ ሁሉ መሠረታቸው ሆነላቸውና።

የስፓንያ መርከቦች አንዳንዴ በመውጅ ትይዘው በጃፓን ዳር ላይ ሲሰበሩ በዚህ አጋጣሚ ግንኙነት ከአገሩ መጣ። እስፓንያውያን የክርስትናን ሃይማኖት ወደ ጃፓን ለማስፋፋት ፈልገው ነበር። ነገር ግን ተፅእኖ ወደ ጃፓን ለመዘርጋት የተደረገው ጥረት ከ"ኢየሱሳውያን" ወገን ብርቱ ተቃውሞ አገኘ፤ እነኚህ ወንጌሉን በአገሩ ውስጥ በ1541 ዓ.ም. ስብከት ጀምረው ነበርና። ከዚያ በላይ ፖርቱጊዞችሆላንዶች ከጃፓን ጋር ስለነበራቸው መገበያየት ከስፓንያ ምንም ውድድር ለማየት አልወደዱም ነበር።

1601 የስፓንያ ታላቅ መርከብ ሳን ፍራንሲስኮ ከማኒላ ወደ ሜክሲኮ ሲሄድ መውጅ አጋጥሞት በጃፓን ጠረፍ ላይ በቶክዮ ዙሪያ በቺቦ ሲጠፋ መርከበኞቹ በኗሪዎች አማካይነት ድነው ስላምታ ይሰጡና የመርከቡ አለቃ ሮድሪጐ ደ ቪቨሮ ከሾጉን (ደጃዝማች) ቶኩጋዋ ኢኤያሱ ጋራ ተገናኙ።

ኅዳር 23 ቀን 1602 ዓ.ም. የስምምነት ውል ተፈራርመው፣ እስፓንያውያን በምሥራቅ ጃፓን ውስጥ አንድ ፋብሪካ ለመሥራት፣ የማዕድን ሠራተኞች ከ"አዲስ ስፓንያ" (ሜክሲኮ) ወደ አገሩ ለማስገባት፣ የስፓንያ መርከቦች አስፈላጊነት እንደሆነባቸው ጃፓንን ለመጎብኘት ተፈቅደው፣ ደግሞ የጃፓን ተልእኮ ወደ እስፓንያ ቤተ መንግሥት እንዲጓዝ ተወሰነ።

በቶክዮ ዙሪያ ይሰብክ የነበረው መነኩሴ ሉዊስ ሶተሎ ወደ አዲስ እስፓንያ (ሜክሲኮ) አምባሳደር ሆኖ እንዲላክ ሾጉኑን አስረዳቸው። በ1602 ሶተሎ ከተረፉት እስፓንያዊ መርከበኞችና ከ22 ጃፓናውያን ጋራ ለሾጉኑ በእንግሊዛዊው ዠብደኛ በዊሊያም አዳምስ በተሠራው መርከብ በሳን ብዌና ቨንቱራ ላይ ተሣፍሮ ወደ ሜክሲኮ ተጓዘ። አዲስ እስፓንያ ደርሶ እንደራሴውን ሉዊስ ደ ቨላዝኮ አገናኘ። እሳቸው ታዋቂውን ዠብደኛ ሰባስትያን ቪዝካይኖ አምባሳደር ሆኖ ወደ ጃፓን ለመላክ ተስማሙ። በተጨማሪ ከጃፓን ወደ ምሥራቅ እንደ ሆኑ የታሰቡትን "የወርቅና የብር ደሴቶች" እንዲፈልግ ልዩ የሆነ ትእዛዝ መደቡት።