መሃመድ አማን

ከውክፔዲያ
መሃመድ አማን

መሐመድ አማን በመካከለኛ ርቀት በተለይ በ፰ መቶ ሜትር የሩጫ ውድድር የሚሳተፍ ኢትዮጵያዊ ነው። በሐገራችን አቆጣጠር ጥር ፪ ቀን ፲፱፻፹፮ ዓ.ም በአሰላ ከተማ የተወለደው መሃመድ እ.ኤ.አ በ2009 እና 2011 የአፍሪካ ታዳጊ አትሌቶች ውድድሮች ላይ በ800 ሜትር አሸናፊ መሆን ችሎ ነበር።

ለንደን ኦሎምፒክስ ተሳትፎ የነበረው መሃመድ ሁለት ዙር ማጣሪያዎችን አልፎ ለፍጻሜ ውድድር በማለፍ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ አትሌት ለመሆን በቅቷል። በፍጻሜው ውድድር ሜዳልያ ሰንጠረዥ ውስጥ መግባት ባይችልም የራሱን እና የኢትዮጵያን ክብረ-ወሰን በማሻሻል ነበር ውድድሩን ያጠናቀቀው። ከኦሎምፒክስ በኋላ በተከፈተው የዳይመንድ ሊግ ውድድር የተሳተፈው መሃመድ በዙሪክ በተካሄደ የ800ሜትር ውድድር ላይ የዓለም ሪከርድ ባለቤቱን ኬንያዴቪድ ሩሺዳን ቀድሞ በመግባት አሸናፊ ሆኗል። በዚህም ውድድር የራሱን እና የኢትዮጵያን ሪከርድ በማሻሻል ነው ያጠናቀቀው። [1]

የውድድር ሪከርድ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ምርጥ ሰዓት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማጣቀሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ "ሞሃመድ አማን በስዊዘርላንድ በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር አሸነፈ". thearadaonline.com (31 Aug 2012). Archived from the original on 28 September 2012. በ31 Aug 2012 የተወሰደ.
በ"Wikimedia Commons"
(የጋራ ፎቶዎች ምንጭ)
ስለ Mohammed Aman የሚገኛኙ
ተጨማሪ ፋይሎች አሉ።