መለስ ዜናዊ
| መለስ ዜናዊ | |
|---|---|
| የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር | |
| ከነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. እስከ ነሐሴ ፲፬ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. | |
| ፕሬዝዳንት | ነጋሶ ጊዳዳ መ/አለቃ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ |
| ቀዳሚ | ታምራት ላይኔ (ተግባራዊ) |
| ተከታይ | ኃይለማሪያም ደሳለኝ |
| የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት | |
| ከግንቦት ፳ ቀን ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. እስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. | |
| ጠቅላይ ሚኒስትር | ተስፋዬ ዲንካ ታምራት ላይኔ |
| ቀዳሚ | ተስፋዬ ገብረ ኪዳን (ተግባራዊ) |
| ተከታይ | ነጋሶ ጊዳዳ |
| ሌላ ስም | ለገሠ ዜናዊ አስረስ (የትውልድ) |
| የተወለዱት | ሚያዝያ ፴ ቀን ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. አድዋ፣ ኢትዮጵያ |
| የሞቱት | ነሐሴ ፲፬ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. ብረስልስ፣ ቤልጅግ |
| የፖለቲካ ፓርቲ | ኢህአዴግ |
| ባለቤት | አዜብ መስፍን |
| ሀይማኖት | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና |
መለሰ ዜናዊ (የትውልድ ስማቸው ለገሠ ዜናዊ አስረስ) (ሚያዝያ ፴ ቀን ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ነሐሴ ፲፬ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም) የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሰው ነበሩ። በአድዋ ትግራይ የተወለዱ ሲሆን ከ፲፱፻፹፯ ዓ/ም አንስተው እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ በኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን በከፍተኛው የአመራር ቦታ ላይ ነበሩ። የኢህአዴግና የሕውሓት ሊቀመንበር በመሆን ኢህአዴግ ስልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ ቆይተዋል።
አቶ መለስ ዜናዊ ኣባታቸው የትግራይ ተወላጅ ሲሆኑ በእናታቸው በኩል ደግሞ ኤርትራዊ ናቸው።
ማውጫ |
ወደ ስልጣን አመጣጥ
አቶ መለስ የሚመሩት ሕውሓት የኮሎኔል መንግስቱ ኅይለ ማርያምን አምባ ገነናዊ መንግስት በትጥቅ ትግል ሲታገሉ ከነበሩ ድርጅቶች አንዱ ነው። አቶ መለስ የሕወሓት አመራር ኮሚቴ መሪ ሆነው በ1971 ተመረጡ ቀጥሎም በ1975 የድርጅቱ ማእከላዊ ኮሚቴ ሊቀመንበር ሆኑ። የደርግ መንግሥት ከወደቀም ጀምሮ የሕውሓትና የኢህአዴግ ሊቀ መንበርም ናቸው። ኢህአዴግ የአራቱ ፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የትግራይና የደቡብ ሀዝቦች ብሔር ውህደት ነው። ወደ ስልጣን ሲመጡ በጊዜው ላቋቋሙት ጊዜያዊ መንግስት ፕረዚዳንት ሆነው ካገለገሉ በሗላ 1985 ለመጀመሪያ ጊዜ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነውም ተመረጡ። በጊዜው የፕረዚደንትነቱን ቦታ የተረከቡት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ናችው። በመቀጠልም አቶ መለስ ከባድ ውዝግብ ባስነሳው የ1997 ግንቦት ምርጫ አሸናፊ ሆነው ለሁለተኛ ጊዜ በስልጣን ላይ ይገኛሉ። ጠ/ሚ መለስ በመላው አለም በአምባገነንነት ከሚታወቁ መሪዎች አንዱ ናቸው።በስልጣን ላይም 17 ዓመታት በላይ ቆይተዋል።
የሽግግር መንግስታቸው
የመንግስቱ ኃይለ ማርያምን መሸነፍ ተከትሎ አዲስ አበባን የተቆጣጠረው ኢአሓዴግ መንግስትን ሲያቋቁም ብሔረሰቦችን መሰረት ባደረገ ፓርላማ ስለነበረ ቀድሞ ያልታየና አዲስ ስለነበረ ብዙዎቹን ግራ አጋብቶ ነበር። የሽግግሩ መንግስት በጊዜው ኢህአዴግ ያሰባሰባቸው ድርጅቶች ብቻ ጎልቶ የታዩበት ስለነበረ አሰባሳቢነት የመጡ ስለነበር ከትችትና ከተቃውሞ አላመለጠም።
የኢህአዴግ ደጋፊዎች
በአምባ ገነኑ ደርግ ስር ተጨቁኖ ለነበረው ድሃ ኢትዮጵያዊ የኢህአደግ ወደ ስልጣን መምጣት ከ«የምስራች» ና ሌላ አማራጭ ስላልነበር የኢሕአዴግን መንግስት ሕዝቡለመቀበል ተገደደ ። ከዚህም የተነሳ ኢህአዴግ ይህ ነው የተባለ ተቃውሞ አልገጠመውም። ኢሕአዴግን ሲረዱ የነበሩ የአረብና የምዕራባውያን መንግስታት ከጎንህ አለን በማለት በብዙ ትግል ስልጣን የተቆናጠጠውን ኢህአደግን በሁለት እግሩ አንዲቆም አስችለውታል። የአቶ መለሰ ዚናዊ መንግስት የታገለለትን ዓላማ ስቶ ዲሞክራሲንበማፈን የነጻ ፕሬስ አፈና በማካሄድና የብአዊ መብት ረገጣ ስላበዛ ብዙ የምዕራባዊያን ድጋፍና ከማጣቱም በላይ የብዙ ሺ ኢትዮጵያዊያን ለስደት ዳርጎአል። ሆኖም ዓለም አቀፉን ሽብርተኛ ለመታገል ቃልበገቡት መሰረት ሱማሌን በመውረሩ ምክንያት በጆርጅ ቡሽ የምትመራ አሜሪካ ቀንደኛና ዋነኛ የኢህአዴግ ደጋፊ ሆና ቀርታለች።
የኢህአዴግ ተቃዋሚዎች
ምንም እንኳ በደርግ የግፍ አገዛዝ የተማረረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ኢህአዴግን ለመቀበልና አብሮ ለመስራት ወደ ኋላ ባይልም ውሎ ሲያድር ግን በኢህአዴግ የአገር ውስጥ ፖሊሲ መከፋቱ አልቀረም። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ብሎ ራሱን የስየመው ቡድን ከኢህአዴግ ጋር በመቃቃሩ ራሱን ከፓርላማውና ከካቢኔው አግልሎ ወደ ትጥቅ ትግሉ ተመለሰ።
ጠ/ሚ መለስ የኤርትራን የመገንጠል ጥያቄ ያለምንም ማንገራገር መፍቀዳቸው ብቻ ሳይሆን ሁሉም ብሔረሰብ እንዲገነጠል የሚያስችለውን አንቀጽ በሕገ መንግስታቸው በማካተታቸው በተለይ በምሁራን ዘንድ የከረረ ተቃውሞ አስነስቶባቸዋል። ሁሉም በክልሉ በቋንቋው ይማር የተሰኘው ፖሊሲያችውም በብዙዎች ዘንድ ጥርጣሬና መከፋፈልን በመፍጠሩ በሀገርና ከሀገር ውጭ በተደጋጋሚ የተቃውሞ ሰልፎች ተካይዶባቸዋል።
በ1997 አጋማሽ ጠቅላላ ምርጫ ሲደረግ ከተለያዩ የፖለቲካ ህቡዕ ፓርቲዎች የተውጣጣ ቅንጅት የተሰኘ ጥምር የፖለቲካ ፓርቲ እንደ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ተወዳደረ። በውጤቱም የዓለም ታዛቢዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ከተማ ከመቶ 97 እጁ መራጭ የተቃዋሚውን ፓርቲ ቅንጅትን መረጠ። በውጤቱ የተደናገጠው የአቶ መለስ መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ የአዲስ አበባን ፖሊስ በፌዴራል ቁጥጥር ስር አዞረ። የአዲስ አበባ ምክር ቤትንም በኦሮሚያ መስተዳደር ስር እንዲተዳደር አዲስ ድንጋጌ አወጣ።
ይሁን እንጂ ብዙም ገለልተኛ ታዛቢ በሌለበት ከአዲስ አበባ ውጪ ኢሕአዴግ 90 በመቶ ማሸነፉ ስለታወጀ ተቃዋሚዎች አድልዎ ተደርጎብናልና ምርጫው እንደገና ይጣራ ብለው ለከፍተኛ ፍርድ ቤት የክስ ማመልከቻ በማስገባታቸው ማጣሪያ ተካሄደ። ተቃዎሚዎች በጠቅላላው የምርጫ ውጤት ባለመስማማታቸው ያሸነፉበትን የፓርላማ ወንበር ባለመቀበል የገዢው ፓርቲ በበላይነት ከተቆጣጠረው ፓርላማ ራሳቸውን አገለሉ።
ሚሥስ አና ጎሜዝ የተባሉ የአውሮፓ ታዛቢ ቡድን መሪ ምርጫው አድልዎና ጫና እንደነበረበት ለዓለም ሕዝብ ምስክርነታቸውን ተናገሩ። አብዛኛዎቹ ታዛቢዎች (አፍሪካ ሕብረት አና የጂሚ ካርተርማእከል) ምርጫው በኢትዮጲያ ከተካሄዱ ምርጫዎች በጣም የተሻለ መሆኑን መሰከሩ። በሺ የሚቆጠሩ የቅንጅት ደጋፊዎች በዋና ዋና ከተማዎች በመውጣት ሰላማዊ ሰልፍ በቁጣ በሚገልጹበት ጊዜ ቁጥሩ በርካታ የሆነ ሕዝብ በፖሊስ በቀጥታ በተተኮሰ ጥይት ሕይወቱን አጥቶአል። የአቶ መለስ መንግስት አብዛኛዎችን በህዝብ የተመረጡ የቅንጅት ፓርቲ አባላትንና በሺህ የሚቆጠሩ አባላትን ባገር ክህደት አና መንግስትን ለመገልበጥ በመሞከር ከሰሳቸው። 2 ዓመት በፈጀ የፍርድ ሂደትም ፍርድ ቤቱ የቅንጅት መሪዎችን አገርን በመክዳት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው አገኛቸው ። ይሁን እንጂ ሁሉም የ ቅንጅት መሪዎችና አብዛኛው ደጋፊ አባላት ጥፋታቸውን አምነው ይቅርታ በመጠየቃቸው ከእስር ነጻ ወጡ።
|
|
|
|---|---|
| ንጉሠ ነገሥት መንግሥት (1934-1966) | መኮንን እንዳልካቸው · አክሊሉ ሀብተ-ወልድ · እንዳልካቸው መኮንን · ሚካኤል እምሩ |
| ደርግ (1966-1979) | (ማዕረጉ ተሠረዘ) |
| የኢት. ሕዝባዊ ዲሞ. ሪፐብሊክ (1979-1983) | ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ · ሃይሉ ይመኑ* · ተስፋዬ ድንካ* |
| የኢት. ፌዴራላዊ ዲሞ. ሪፐብሊክ (1983-አሁን) | ታምራት ላይኔ* · መለስ ዜናዊ · ኃይለማርያም ደሳለኝ |
|
*ተግባራዊ
|
|