መሐሙድ አህመድ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሐሙድ

መሐሙድ አህመድ (፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ተወለደ[1]) ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ዘፋኝ ሲሆን ብዙ ዘመናዊ የሙዚቃ ስራወችን በማቅረብ ይታወቃል። መሐሙድ በድምፁ ታላቅነት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካና በአውሮፓ ትልቅ ክብርና ዝና ያለው አርቲስት ነው።[1]

[ለማስተካከል] የህይወት ታሪክ

መሐሙድ አህመድ በአዲስ አበባ ከተማ አሜሪካን ግቢ (መርካቶ) በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ተወለደ። በየዓመቱ በሚመጣው የቡሄ ጨዋታ ላይ የድምፁን ምንነት ያሳወቀው መሐሙድ በወቅቱ እነ ጥላሁን ገሠሠ የሚያሰሙትን ዘፈን በሚማርበት የአርበኞች ት/ቤት ውስጥ ሲዘፍን የሰሙት አስተማሪው ድምፁን ስለወደዱለትና በየዓመቱ በሚከበረው የወላጆች ቀንም ይዘፍን ስለነበር ወደ ሙዚቃው ዓለም በዚሁ የተነሳ ለመግባት ችሏል።[1]

እነ ጥላሁን ገሠሠ፣ ታምራት ሞላተዘራ ኃ/ሚካኤል እና ሌሎችም በሚጫወቱበት አሪዞና በሚባል የምሽት ክበብ ውስጥ በሌላ ሥራ ተቀጥሮ ይሠራ ስለነበር የእነዚህን አንጋፋ ዘፋኞች ሙዚቃ በማጥናትና በመዝፈን ይጫወት ስለነበር የዘፈን ችሎታውን ያዩት ግብፃዊ የምሽት ክበቡ ባለቤት አበረታትተውት እነ ጥላሁንን በማጀብ እንዲሠራ ፈቀዱለት። ሻለቃ ግርማ ሀድጉ ግጥምና ዜማ ፈልገው አውጥተውለት የመጀመሪያውን «ጭቅጭቁ ቀርቶ» የሚለውን ዘፈን ዘፈነ።[1]

ከዚያም አሪዞና ሲዘጋ ሾፌሮች ቡና ቤት ወደ ሚባለው የምሽት ክበብ በመሄድ የነ ገላን ተሰማና የታምራት ሞላን ዘፈኖች ሲጫወት ለመቀጠር እንዲችል በአዳራሹ ውስጥ ለተሰበሰበው ሕዝብ ለፍርድ ይቀርባል። በዚህን ጊዜ «ተስፋ አትቁረጪ» እና «የቡጊ ጨዋታ» የተባሉትን ዘፈኖች ደጋግሞ ተጫውቶ ለመቀጠር ቻለ። በተመሳሳይ ሁኔታም ጃንሜዳ በሚገኘው የክብር ዘበኛ የሠራዊቱ ሆስፒታል ውስጥ ለሠራዊቱና ለቤተሰቦቻቸው በየ፲፭ ቀናት የሙዚቃ ትርኢት ስለሚቀርብ ከዚያም ለድጋሚ ፈተና ቀርቦ በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. በሲቪልነት ተቀጠረ። መሐሙድ ካለፈባቸው የችግር ሕይወት በተጨማሪ የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራ ትልቁ ት/ቤቱ እንደነበረም ይናገራል።[1]

[ለማስተካከል] የሥራዎች ዝርዝር

የመሀሙድ የመጀመሪያ ዘፈኑም «አላወቅሽልኝም» የተባለው የጉሮሮው መክፈቻ ሲሆን «ጠይቀሽ ተረጂ» እና «የፍቅር አዳራሽ» የተባሉት ዘፈኖቹም ለመድረክ ከመቅረባቸው በፊት ለግሩንዲንግ ተሽጠው በቴፕ የተቀረፁ ሥራዎቹ ነበሩ።[1]

[ለማስተካከል] ማጣቀሻዎች

  1. ^ ናሽናል ቢብሊዮግራፊ ቡድን፣ የአንጋፋ አርቲስቶች መዝገበ የሕይወት ታሪክ፣ መጋቢት ፳፻፣ ገጽ 23-24
የኔ መሣርያዎች

Variants
Actions
የማውጫ ቁልፎች
ጠቃሚ መሣሪያዎች
በሌሎች ቋንቋዎች