ማሲንቆ

ከውክፔዲያ
መሰንቆ

መሰንቆ (ወይም ጭራ ዋጣ) ባለ አንድ ክር የሙዚቃ መጫወቻ ሲሆን እንደ ቫዮሊን በደጋን ሲመታ የሙዚቃ ቃና ይሰጣል።

አሰራር ስማቸው[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አንድ የፍየል ወይንም የበግ ቆዳ ያስፈልጋል፤ እንዲሁም የወይራ እንጨት እንዲሁም የፈረስ ወይንም የበሬ ጅማት ያስፈልጋል።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የመሰንቆን ከየት መጣ በቅጡ ለመረዳት አዳጋች ቢሆንም በአንድአንድ የምዕራብ አፍሪካ እና መካከለኛ ምሥራቅ ሀገራት በድምጽ የሚመሳሰሉ አካላዊ ቅርጻቸው ግን ልዩነት ያላቸው መሣሪያዎች አሉ። መሰንቆ በቤተ መንግሥት መኳንንትን ለማስደሰት፣ ጦርነት የሆነ እንደሆነ ደግሞ ወታደሩን በስሜት ለመቀስቀስ ይጠቀሙበት ነበር። በማዕረግ ደረጃም ሊቀ መኳስ በሚል ስያሜ ሹመት ይሰጣቸው ነበር። ለምሳሌ ያህል በዓድዋ ጦርነት ተሳትፈው የነበሩት፤ የወሎው ንጉሥ የራስ ሚካኤል ባለሟል ሀሰን አማኑ ጥይት ባይተኩሱም በግጥሞቻቸው ጣልያንን መደቆሳቸውን ታሪክ ይመሰክራል። ወታደሩን ከማነሳሳት አንጻር የአዝማሪዎቹ ድርሻ ከፍተኛ ነበር። ለዚያም ነው በሁለተኛው የኢጣሊያ ወረራ አዝማሪዎች ከያሉበት ተሰብስበው ሕይወታቸው እንዲያልፍ የተደረገው።

ሙዚቃዊ ባህርዩ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

መሰንቆ ሀገር አቀፋዊ የአሠራር ስታንዳርድ የለውም። በመሆኑም የጭራው ብዛት እና ርዝመት፣ የተሠራበት የእንጨት ዓይነት፣ የተጠቀምነው የቆዳ ዓይነት እና የጭራውን ፍሪክሽን ለመቀነስ የተጠቀምንበት ዕጣን ለድምጹ መለዋወጥ የራሳቸውን አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።