ሞንሮቪያ

ከውክፔዲያ
የሞንሮቪያ አቀማመጥ በላይቤሪያ

ሞንሮቪያላይቤሪያ ዋና ከተማ ነው።

ሞንሮቪያ ያለበት ልሳነ ምድር ከጠፈር በሌሊት ሲታይ

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 550,000 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 06°18′ ሰሜን ኬክሮስ እና 10°47′ ምዕራብ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

ፖርቱጋል መርከበኞች በ1560 ዓ.ም. ገዳማ ቦታውን 'ካፕ ሜዙራዶ' በሰየሙት ጊዜ ብዙ ኗሪዎች ይገኙ ነበር።

1813 ዓ.ም. ነጻ ጥቁሮች ከአሜሪካሸርብሩክ ደሴት (ዛሬ ሲዬራ ሌዎን) ሠፈሩ። ነገር ግን ይህ አልተከናወነምና ብዙዎች ሞቱ። ስለዚህ በ1814 ዓ.ም. ሌላ መርከብ ይዞአቸው ወደ ካፕ ሜዙራዶ አዲስ ሠፈር ጀመሩ። ስሙ ክራይስቶፖሊስ (ከግሪክ 'የክርስቶስ ከተማ' ማለት ነው) ሆነ። በ1816 ዓ.ም. ግን አዲስ ስሙ ሞንሮቪያ ሆነ፤ ይህም በወቅቱ አሜሪካዊ ፕሬዚዳንት በጄምስ ሞንሮ ትዝታ ተደረገ። ከአለሙ ዋና ከተሞች (ከዋሺንግቶን ዲሲ በቀር) እሱ ብቻ ለአሜሪካዊ ፕሬዚዳንት ስም ተሰየመ።