ሰናፌ

ከውክፔዲያ
ሰናፌ - በ1860ዓ.ም. በእንግሊዝ ጦር ፎቶ አንሽወች እንደተነሳ
ሰናፌ

ሰናፌኤርትራ ውስጥ የምትገኝ የገበያ ከተማ ናት። በኤርትራና ኢትዮጵያ ጦርነት ተጐድታለች። በዙሪያው የሚኖሩት ሳሆና ትግሬ ሕዝብ አሉ። የሰናፌ መጀመርያ ስም ሀኪር ነበረ። አካባቢው የመተ የመጠራ ታሪካዊ ቦታና እንዲሁም የደብረ ሊባኖስ ገዳም(ኤርትራ) በመያዙ ይታወቃል። ታሪካዊ ቦታ ሲባል የመጀመርያዎቹ (በ6ተኛው ክፍለ-ዘመን)ብብዛት መጥተው እያስተማሩ እስከ ሞቃድሾ የደረሱ ጻድቃናት ለመጀመርያ መጠራ እንዳረፉ ትክክለኛው ታሪክ ያረጋግጠዋል። ከዚያም ኣልፎ የበለው ከለው ቤተ መንግስት ነበር ሲሆን ከልደተ ክርስቶስ በፊት በጥሩ ሁኔታ ተገንብቶ የነበረ እስክ ኣሁን ቅርሱ ያልተደመሰሰ ግን ደግመ ታሪካዊ ቦታ ከመባል ኣልፎ ምርምር ያልተካሄደለት ቦታ ከሰናፌ 3 ኪ.ሜትር ርቆ ይገኛል። ብኣጠቃላይ ሰናፌና ዙርያዋ የታሪክና የጥንታዊ ኣድባራት መሆኑ በእርግጠኝነት መነገር ይቻላል።