ሰንደቅ ዓላማ በቋሚ ላይ እንዲውለበለብ የሚሰቀል ጨርቅ ነው። በድሮ ጊዜ መረጃ መለዋወጥ ዋነኛ ጥቅሙ ነበረ። በአሁኑ ጊዜ ግን የአንድን ሀገር ወይም ድርጅት ለመወከል ያገለግላል።
አቶ ከበደ ሚካኤል "ታሪክና ምሳሌ - ፩ኛ መጽሐፍ" በተባለው ድርሰታቸው ላይ፦ ሰንደቅ ዓላም የነጻነት ምልክት የአንድ ሕዝብ ማተብ፤ የኅብረት ማሰሪያ ጥብቅ ሐረግ ነው። «ተመልከት ዓላማህን፣ ተከተል አለቃህን።» ብለው አስፍረውታል።
የዓለም ባንዲራዎች
-