ሰንደቅ ዓላማ
ከውክፔዲያ
ሰንደቅ ዓላማ በቋሚ ላይ እንዲውለበለብ የሚሰቀል ጨርቅ ነው። በድሮ ጊዜ መረጃ መለዋወጥ ዋነኛ ጥቅሙ ነበረ። በአሁኑ ጊዜ ግን የአንድን ሀገር ወይም ድርጅት ለመወከል ያገለግላል።
አቶ ከበደ ሚካኤል "ታሪክና ምሳሌ - ፩ኛ መጽሐፍ" በተባለው ድርሰታቸው ላይ፦ ሰንደቅ ዓላም የነጻነት ምልክት የአንድ ሕዝብ ማተብ፤ የኅብረት ማሰሪያ ጥብቅ ሐረግ ነው። «ተመልከት ዓላማህን፣ ተከተል አለቃህን።» ብለው አስፍረውታል።
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማችን አረንጓዴ፤ ብጫና ቀይ ሦስት ቀለማት ናቸው። ምሳሌያቸውም አረንጓዴው ተስፋ፣ ልምላሜና ሀብት፤ ብጫው ሃይማኖት፣ አበባና ፍሬ፤ ቀዩ ፍቅር፣ መሥዋዕትነትና ጀግንነት ነው።