ሰኸተፒብሬ

ከውክፔዲያ
ሰኸተፒብሬ
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1798-1796 ዓክልበ. ግ.
ቀዳሚ ሰመንካሬ ነብኑኒ
ተከታይ ሰዋጅካሬ
ሥርወ-መንግሥት 13ኛው ሥርወ መንግሥት

ሰወሰኽታዊ ሰኸተፒብሬ ላይኛ ግብጽ2ኛው ጨለማ ዘመን (13ኛው ሥርወ መንግሥት) ከ1798 እስከ 1796 ዓክልበ. ግድም ድረስ የገዛ ፈርዖን ነበረ። የሰመንካሬ ነብኑኒ ተከታይ ነበረ። ስሙ «ሰኸተፒብሬ» ትርጉም ከግብጽኛ «የን ልብ የሚያረጋጋ» ማለት ነው።

አንድ ማሕተም ቅርስ የሰኸተፒብሬ ስያሜ በሃይሮግሊፍ እና የጌባል (በፊንቄ) ገዥ ያኪን-ኢሉ ስም በኩነይፎርም ጽሕፈት አንድላይ ያሳያል።[1]

ሕልውናው ደግሞ ከአንድ ጽላት ተረጋግጧል። ይህም ጽላት በሲና ልሳነ ምድርኩልእርሳስ ማዕድን ቦታ ተገኘ። በኋላ ዘመን በተጻፈው በቶሪኖ ቀኖና ነገሥታት ዝርዝር ላይ የሆተፒብሬ ስም ደግሞ «ሰኸተፒብሬ» ስለሚጻፍ፣ አንዳንድ ሊቃውንት ሁለቱን አደናግረዋል። በአቶ ራይሆልት ግመት ተከታዩ ሰዋጅካሬ ነበር።

ቀዳሚው
ሰመንካሬ ነብኑኒ
ግብፅ (ጤቤስ) ፈርዖን
1798-1796 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ሰዋጅካሬ

ዋቢ ምንጭ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ የሰኸተፒብሬ ማኅተም
  • K.S.B. Ryholt: The Political Situation in Egypt during the Second Intermediate Period, c. 1800 – 1550 BC, Carsten Niebuhr Institute Publications, vol. 20. Copenhagen: Museum Tusculanum Press, 1997 (እንግሊዝኛ)