ቀንጠፋ

ከውክፔዲያ
ቀንጠፋ

ቀንጠፋ ወይም ቆንጥር (Pterolobium stellatum) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሌላ ዝርያ፣ የግራር ዛፍ አይነት Acacia brevispica ደግሞ «ቀንጠፋ» ተብሏል።

ሁለቱም በአተር አስተኔ ወይም «አባዝርት» አስተኔ ናቸው።

አስተዳደግ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በምሥራቅ አፍሪካና በየመን ይገኛል። በድንጋያማ ዳገት፣ በወንዝ ደለል፣ በጫካ ዳርቻ ይገኛል።

የተክሉ ጥቅም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ለቊጥቋጦ-ኣጥር ይስማማል። ቡቃያዎቹም ለከብት መኖ ይሰበሰባሉ።

በኢትዮጵያ፣ የተደቀቀው ልጥ ጭማቂ በቆዳ ፋቂ ለማቀላት ተጠቅሟል።[1] ቅጠሎቹም ሲደቀቁ ጨለማ-ቀይ ቀለም ይሠራል።

ትኩስ ቅጠሎቹ ለመድሃኒት ይኘካል፣ ለምሳሌ የሳምባ ነቀርሳን ወይም ተመሳሳይ የመተንፈስ ችግሮችን ለማከም።[2]

የቀንጠፋው ፍሬ ለማስታወክ እንደሚጠቀም ተዘግቧል።[3]

  1. ^ Jansen, P.C.M. & Cardon, D. (2005). Dyes and Tannins. Plant resources of tropical Africa. 3. Prota. pp. 134–135.
  2. ^ አማራ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  3. ^ የፍቼ፣ ኦሮሚያ ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 2006 ዓም ከዓቢዩ እኒየው እና ሌሎች፣ ጎንደርና አዲስ አበባ ኡኒቨርሲቲዎች ሥነ ፍጥረት ኮሌጆች