ቀዳማዊ፡ኃይለ፡ሥላሴ

ከWikipedia

ዘልለው ለመሐድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ፤ ንጉሠ ነገሥት ፲፱፻፳፫ - ፲፱፻፷፮

ግርማዊ፡ ቀዳማዊ፡ ዓፄ፡ ኃይለ፡ ሥላሴ፡ ንጉሠ፡ ነገሥት፡ ዘኢትዮጵያተፈሪ መኰንን ስመ-መንግሥት ነበር። ሞዓ፡ አንበሣ፡ ዘእምነገደ፡ ይሁዳ፡ ሥዩመ፡ እግዚአብሔር፣ የሚለው የሰሎሞናዊው ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር።

ተፈሪ መኰንን ሐምሌ 16 ቀን 1884 ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ።

1899ሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ1903 ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር፣ ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ1909 ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም 27 ቀን 1921 ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ1922 ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት 23 ቀን1923 ዓ.ም.፣ ብዙ የውጭ ልኡካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ።

በንግሥ በዓሉ ዋዜማ፤ ጥቅምት 22 ቀን የትልቁ ንጉሠ ነገሥት የዳግማዊ ዓጼ ሚልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አጠገብ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ።

ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት 8 ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ስርዐቱ በዓለም ዜና ማሳረጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል።

ዓጼ ኅይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት 23 ቀን 1924 ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ።

1928 ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የአለምን እርዳታ በመጠይቅ ተናገሩ። የአለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ1932 ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ1933 ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። አጼ ኅይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት አመት በኋላ ነበረ።

1955 ዓ.ም. ግርማዊ የአፍሪካ አንድነት ድርጅትአዲስ አበባ እንዲጀመር ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ1958 ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ1967 ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣኔ ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው አመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ።

[ለማስተካከል] ጥቅስ

<< አንዳንድ ሰዎች የሕይወቴን ታሪክ ጽፈው ባለማወቅ ወይም በመሳሳት ወይም በመቀኝነት ዕውነትን አስመስለው ለሌሎች እንዲመስል ቢሞክሩም የዕውነተኛውን ነገር ከሥፍራው ሊያናውጡት አይችሉም። >>
-- ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ (መቅደም)
የኔ መሣርያዎች