ቀዳማዊ፡ኃይለ፡ሥላሴ
ከWikipedia
ግርማዊ፡ ቀዳማዊ፡ ዓፄ፡ ኃይለ፡ ሥላሴ፡ ንጉሠ፡ ነገሥት፡ ዘኢትዮጵያ፣ የተፈሪ መኰንን ስመ-መንግሥት ነበር። ሞዓ፡ አንበሣ፡ ዘእምነገደ፡ ይሁዳ፡ ሥዩመ፡ እግዚአብሔር፣ የሚለው የሰሎሞናዊው ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ኦፊሴላዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር።
ተፈሪ መኰንን ሐምሌ 16 ቀን 1884 ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ።
በ1899 የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ1903 ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቄሳውንት ስለዚህ አልወደዱዋቸውም ነበር፣ ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ1909 ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ።
[ለማስተካከል] ጥቅስ
- << አንዳንድ ሰዎች የሕይወቴን ታሪክ ጽፈው ባለማወቅ ወይም በመሳሳት ወይም በመቀኝነት ዕውነትን አስመስለው ለሌሎች እንዲመስል ቢሞክሩም የዕውነተኛውን ነገር ከሥፍራው ሊያናውጡት አይችሉም። >>
- -- ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ (መቅደም)

