ቅኝ ግዛት

ከውክፔዲያ

ቅኝ ግዛት ማለት የአንድ ሃገር ህዝቦች የሌላውን ሃገር ህዝቦች በቁጥጥር ስር በማዋል የሚደረግ ግዛትን የማስፋፋት ስራት ነው። በዋናነት ቅኝ ግዛት የሚገለጸው ከ15ኛው እስከ 20ኛ ክ/ዘመን ያለውን የአውሮፓ ሀገሮች የአፍሪካን፣ ሰሜን አሜሪካን እና የእስያ ሃገሮች የተቆጣጠሩበትን ዘመን ነው። ጣሊያን ኢትዮጵያ ላይ የቅኝ ግዛት ሙከራ ከአንዴም ሁለት ጊዜ ያደረገች ሲሆን ጀግኖቹ ኢትዮጵያውያ አርበኞች ባደረጉት የሞት ሽረት ተጋድሎ አሸንፈው ባንዲራዋ በነፃነት ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ አድርገዋል።