በዓሉ ግርማ

ከWikipedia

ዘልለው ለመሐድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
በዓሉ ግርማ (1928 - 1976 ዓ.ም.)
በዓሉ ግርማ (1928 - 1976 ዓ.ም.)

ደራሲ በዓሉ ግርማ በኢላባቡር ክፍለ ሀገር ሱጴ በምትባል ሥፍራ በ1928 ዓ.ም ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ የአንደኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን በልዕልት ዘነበወርቅትምሕርት ቤት ፤ ሁለተኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን ደግሞ በጄኔራል ዊንጌት ትምሕርት ቤት አጠናቀዋል። ከዚያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፖሊቲካል ሳይንስ እና ኢንተርናሽናል ሪሌሽንስ የ ቢ.ኤ. ዲግሪ ያገኙ ሲሆን፤ በዚሁ ተመሳሳይ መስክ ከአውሮፓ የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።

ደራሲ በዓሉ ግርማ በተለይ በልብ ወለድ እና በፈጠራ የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች ከታወቁት የኢትዮጵያ የዘመኑ ደራሲዎች መካከል ተወዳጅነትና ዝናን ያተረፉ ዕውቅ ደራሲ ነበሩ። ከጻፏቸው በርካታ ድርሰቶቻቸው ውስጥ "ከአድማስ ባሻገር" የተሰኘው መጽሐፋቸው በሩስያ ቋንቋ ተተርጉሞ በቀድሞዋ የሶቪየት ሶሽያሊስት ሕብረት ሪፑብሊክ ቀርቧል። በተጨማሪም በጋዜጠኝነት ሙያም ስማቸውን ያስጠሩ፤ ሙያቸውንም ያስከበሩ ደራሲ ነበሩ። "የዛሬይቱ ኢትዮጵያ" ጋዘጣ፤ የመነን መጽሔት፤ የአዲስ ረፖርተር መጽሔት፤ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በመሆን ከመሥራታቸውም ባሻገር፤ ብዙ ወጣት ጋዜጦችን ለማፍራት ጥረት አድርገዋል። አዲስ ሪፖርተር የተባለውን መጽሔትም ደረጃው ከፍ እንዲልና በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲገመገም አድርገዋል። በጋዜጠኝነት ሙያቸው በኢትዮጵያ ራዲዮ ሠርተዋል።

ደራሲ በዓሉ ግርማ ለኢትዮጵያ ሥነጽሑፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱና ብዙ ሥራዎችን ያቀረቡ ሲሆን፤ የመጨረሻው መጽሐፋቸው "ኦሮማይ" በመባል ይታወቃል። ይኼውም መጽሐፍ በወቅቱ በነበረው የደርግ መንግሥት ሊደገፍ ባለመቻሉ በ 1976 ዓ.ም. ለደራሲው ሕይወት መጥፋት መንስኤ ሊሆን በቅቷል። [1]

[ለማስተካከል] ድርሰቶች

  • ከአድማስ ባሻገር
  • የኅሊና ደወል
  • የቀይ ኮከብ ጥሪ
  • ሐዲስ
  • ደራሲው
  • ኦሮማይ

[ለማስተካከል] ማስታወሻ

  1. ብሔራዊ ቢብሎግራፊ (የደራሲያን አጭር የሕይወት ታሪክ) 1998 ዓ.ም.
የኔ መሣርያዎች