ቡሩንዲ
|
Republika y'u Burundi |
||||||
|---|---|---|---|---|---|---|
|
||||||
| ብሔራዊ መዝሙር: ቡሩንዲ ብዋኩ (የኛ ብሩንዲ) | ||||||
|
ቡሩንዲ በቀይ ቀለም
|
||||||
| ዋና ከተማ | ቡጁምቡራ |
|||||
| ብሔራዊ ቋንቋዎች | ኪሩንዲ ፈረንሣይኛ |
|||||
| መንግሥት ፕሬዚዳንት |
ፒዬር ንኩሩንዚዛ |
|||||
| የመሬት ስፋት አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.) |
27,830 (146ኛ) |
|||||
| ገንዘብ | የቡሩንዲ ፍራንክ | |||||
| የሰዓት ክልል | UTC +2 | |||||
| የስልክ መግቢያ | +257 | |||||
የቡሪንዲ ሪፕብሊከ (ቀድሞ ኡሩንዲ (urundi) የተባለ ሲሆን) በአፍሪካ ውስጥ የምትግኝ ተንሽ አገር ናት። በሩዋንዳ፥ ታንዛኒያ፥ እና በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ትዋሰናልች። አገሯ ወደብ-የለሽ ብትሆንም ከታንጋንዪካ ሐይቅ ጋር ትዋሰናለች። የቡሩንዲ ዋና ከተማ ቡጁምቡራ ሲሆን የሀገሩ የህዝብ ብዛት ወደ 8.7 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል።
የቱዋ፣ ቱትሲና ሁቱ ብሔሮች በቡሩንዲ ለአምስት ምእተ ዓመታት ያህል ኖረዋል። የቱትሲ ሕዝብ ቡሩንዲን በየንጉሥ መንግሥትነት ለሁለት መቶ ዓመታት ያህል መርቷል። ግን በ፳ኛው ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ፣ አካባቢው በጀርመንና ቤልጅግ ቁጥጥር ስር ላይ ኖሯል። ቡሩንዲና ሩዋንዳም አንድ ላይ ሩዋንዳ ኡሩንዲ እየተባሉ በቅኝ ግዛት ጊዜ ተጠርተዋል።
በአካባቢው የሰፈነው የፖለቲካ ቀውስ በቡሩንዲ የእርስ በርስ ጦርነት ፈጥሮአል። በአሁኑ ጊዜ ቡሩንዲ ፕሬዝዳንታዊ የተወካዮች ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሆና ትመራለች። ከሀገሩ ሕዝብ ውስጥ ፷፪ ከመቶ የሮማ ካቶሊክ እምነት ተከታይና ከ፰ እስከ ፱ ከመቶ እስላም ሲሆን የተቀረው ሌሎች የክርስትና ዕምነቶችን ወይም ባህላዊ ሃይማኖቶችን ይከተላል።
ቡሩንዲ ከዓለም አስር እጅግ ድሀ ሀገራት አንዷ ናት። የዚህ ምክንያት ከሆኑት ውስጥ ጦርነቶች፣ ሙስና፣ የትምህርት አለመስፋፋትና የኤድስ በሽታ ይጠቀሳሉ። የተፈጥሮ ሀብቶቿ መዳብና ኮባልትን ይጨምራሉ። ኤክስፖርት ከምታደርጋቸው ምርቶች መካከል ዋናዎቹ ቡናና ስኳር ናቸው።
ታሪክ [ለማስተካከል]
የመጀመሪያው የቡሩንዲ ነዋሪዎች የፒግሚ ሰዎች ናቸው። ከዛም በባንቱ ሕዝቦች ባብዛኛው ተተክተዋል። በ16ኛው ክፍለ ዘመን ነጻ መንግሥት ነበረ። ከዛ በ1903 እ.ኤ.አ. የጀርመን ቅኝ ግዛት ሆነች። በአንደኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ ወደ ቤልጅግ ተላለፈች።
|
||||||||||||||||||||||||||||