ቢላል
| ይህ መጣጥፍ የውክፔዲያ የአቀማመጥ ልምዶችን እንዲከተል መስተካከል ይፈልጋል። |
የነብዩ ባልደረባዎች ታሪክ ***ቢላል አል -ሀበሽ ***
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው እጀምራለሁ ያ አላህ አንተ ካሳወቅከን በስተቀር እውቀት የለንምና ጠቃሚ እውቀትን ትሰጠን ዘንድ እንማጸንሀለን ::አሜን
ይህ ሰው ኢስላምን ባይቀበል ኖሮ የአሳዳሪውን ግመል ከመጠበቅ ሌላ የህይወት ሚና የሌለው፡ እንኳንስ ከሞተ በሁዋላ ይቅር እና በህይወት ዘመኑም አስታዋሽ አካል የሌለው ተራ ፍጡር ሆኖ በቀረ ነበር።
የሀበሻው ቢላል ኢብኑ ረባህ ውድ ወንድሞች እና እህቶቼ አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ እንደምን አላችሁ ? እኔ አልሀምዱሊላህ እጅግ በጣም ደህና ነኝ። በኢስላም ኒዕማ ውስጥ እምነሸነሻለሁ። ያ አላህ በኢስላም ላይ አኑረኝ :ነፍሴ ከስጋየ ስትለይም በኢስላም ላይ ቀጥ እንዳልኩ እንዲሆን በዱዐ እለምንሀለሁ። ለዛሬው በብርሀን ፍጥነት ተጉዘው በደማቸው ታሪክ ጽፈው ታሪክ ሰርተው ወርቃማ አሻራቸውን ለትውልድ ከተው የነብዩ ባልደረቦች ውስጥ የሀበሻውን ቢላል ይዠላችሁ ስቀርብ በደስታ ነው። ለአንባቢ እንዳይሰለች በ 3 ተከታታይ ክፍል ለማቅረብ እሞክራለሁ ኢንሻአላህ።
[ለማስተካከል] ክፍል አንድ
ቢላል ኢብኑ ረባህ የምስጋና እና የሙገሳ ቃላትን ሲሰማ አንገቱን ይደፋ ነበር እናም አይኖቹን በትዝታ ገርበብ አድርጎ ትናንት ባሪያ የነበርኩ ሀበሻ ነኝ ይላል። እነሱ ግን የእኛ ልዑል ብለው ነበር የሚጠሩት። ኡመያ ኢብን ኸለፍ በመባል የሚታወቅ ቁረይሽ ባሪያ የነበረው ቢላል ነብዩ ሙሐመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም በነብይነት የመላካቸው ወሬ የመካን ህዝብ ሲያተራምስ ከቢላል ጆሮ ደረሰ። የቢላል አሳዳሪ ከእንግዶቹ ጋር ስለ ነብዩ መላክ እና ጣኦታቸውን እንደሚቃወም በንዴት እየተብሰለሰለ እና ሴራ እያውጠነጠነ ሲናገር ሙሐመድ ስለተንሱበት አላማ እና ምን እያሉም እንደሚያስተምሩ ሊቀነጭብ ቻለ።
[ለማስተካከል] ክፍል ሁለት
አዲስ የመጣው ዲን ለአካባቢው እንግዳ እና ስር ነቀል ለማምጣት ያለመ ሙሀመድም ምንም እንኳን ነብይ ነኝ ብለው በመናገራቸው ተቃውሞ የገጠማቸው ቢሆንም ታማኝ :እውነተኛ እና በስነ ምግባር የታነጹ መሆናቸውን ከጠላቶቻቸው ቁንጮዎች አንደበት አድምጧል። «ሙሀመድ አንድም ቀን ዋሽቶ አያውቅም: ጠንቋይም ሆነ እብድ አልነበረም:... ዛሬ ግን እኛ እርሱን በነዙህ ነገሮች መጥራት ይኖርብናል። ወደ እርሱ የሚጎርፉትን ሰዎች መግታት የምንችለው በዚህ መንገድ ነው።» በማለት ዚዶልቱ ቢላል ታዝቧል።
ሙሐመድን የሚቃወሙት በቅድሚያ የአባቶቻቸውን እምነት ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ የቁረይሽን የበላይነት የሚያከስም መስሎ ስለተሰማቸው ነው። ቁረይሽ በመላው አረብ ለጣኦታዊ እምነት ማዕከል በሆነችው በመካ የሚገኝ ነገድ በመሆኑ ተፈሪነቱ እና ከበሬታው የላቀ ነበር። በ 3ኛ ደረጃ በኒ ሀሽም ተብሎ በሚታወቀው የነብዩ ሙሐመድ የዘር ሀረግ ቤተሰብ ላይ ያሳደሩት ቅናት እና ምቀኝነት ነበር። ከበኒ ሀሽም ቤተሰብ ነብይ እና መልእክተና መምጣቱን እንደ ሽንፈት ቆጥረውታል ? ሁሉም ጎሳ እና ቤተሰብ ከራሱ ወገን ነብይ እንዲወጣ ይመኝ ነበር። ከ እለታት አንድ ቀን ቢላል ኢብኑ ረባህ የኢማን ብርሀን ፈነጠቀበት : ምርጫውን ይፋ ማድረግ እንዳለበት ወሰነ። ወደነብዩ ሙሀመድ በመሄድም ለኢስላም እጁን መስጠቱን ይፋ አደረገ። የቢላል መስለም በመካ ምድር ተሰማ። የበኒ ጁመህ መሪዎች በቁጣ ተወጠሩ : በተለይ አሳዳሪው የኢስላም ጠላት ኡመያ ኢብን ኸለፍ ሀበሻዊ ባሪያው መስለሙ እንደ ታላቅ ነውር እና ንቀት ቆጥሮታል። ለዚህም እንዲህ አለ «-ይህ ኮብላይ ባሪያ በመስለሙ ጸሀይ ተመልሳ የምትጠልቅ አይመስለኝም...» ሲል ቁጭቱን ገለጸ።
ቢላል ግን ለኢስላም ብቻ ሳይሆን ለመላው የሰው ዘር የሚያኮራ አቋም ከመውሰድ ወደ ሁዋላ አላለም። አላህ የአንድ ሰው የቆዳ ቀለሙ መጥቆር ከፍተኛውን የኢማን ደረጃ ለማግኘት የሚያግደው እንደማይሆን በቢላል ተምሳሌነት አስተምሯል። ቢላል ለዘመኑ ሰዎች እና ከ እሱ በሁዋላ ለመጣው ትውልድ እንዲሁም እምነቱን ለሚጋሩት እና ለማይጋሩትም ወገኖች ያስተማረው ትምህርት ቢኖር የህሊና ነጻነት እና ሉአላዊነት ምድርን የሞላ ንዋይም ሆእን አሰቃቂ ቅጣት ሊበግረው እንደማይችል ነው። ቢላል እርቃኑን በትኩስ አሸዋማ መሬት ላይ እንዲንከባለል እና ቋጥኝ ድንጋይም ደረቱ ላይ እንዲጫን ተደርጓል። ግን እምነቱን ሊቀይር አልፈቀደም። በተከታታይ እና በተደጋጋሚ ኢ -ሰባአዊ ድርጊት ተፈጽሞበታል። የቁረይሽ ሹማምንት አንድን ባሪያ ሊያሳምኑ እና ወደ ቀድሞው እምነቱ ሊመልሱት ባለመቻላቸው ቁጭት እና ሀፍረት ስለተሰማቸው ክብራቸውን ለመጠበቅ ሲሉ ቢላል ቢያንስ ቢያንስ ስለ አማልክቶቹ ጥቂት በጎ ነገር እንዲናገር ቢጠይቁትም አሻፈረኝ አለ። ህይወቱን ከስቃይ ምናልባትም ከሞት ለማዳን ቢያንስ ስለ አማልክቶቻቸው ከልቡ እንኳ ባይሆን ማመስገን በቂ ነበር። ታላቁ ቢላል ግን ከስጋዊ ህመም መንፈሳዊ የበላይነትን በመምረጡ ለጠላቶቹ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም። ይልቁንም በተደጋጋሚ አሀድ አሀድ ... በማለት የአምላክን አንድነት ያውጅ ነበር። ላት እና ኡዛ የተሰኙ ጣኦታትን እንዲያወሳ ያለመታከት ይጠይቁታል። መልሱ ግን አሁንም አሀድ ...አሀድ ...ነበር። እኛ የምንለውን ደግመህ በል በማለት ይገርፉታል : በምጸታዊ ቃልም እናንተ የምትሉትን ለመናገር ምላሴ አይችልም ይላቸዋል ....