ታሪካዊ አቆጣጠር በየክፍለዘመኑ

ከWikipedia

ዘልለው ለመሐድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ይዞታ

[ለማስተካከል] ከክርስቶስ ልደት በፊት

  • 2700 ገ. የጊዛ ታላቅ እስፊንክስግብጽ ተሠራ።
  • 2360 ገ. - የሱመር ከተማ ላጋሽ አለቃ ኡሩካጊና ያዋጀ ሕገ ፍትሕ በታሪካዊ መዝገብ እስከምናውቀው ድረስ መጀመርያ የሕገ መንግሥት ሰነድ ነው።
  • 2330 ገ. ኤላም1 ሳርጎን ወደ አካድ መንግሥት ተጨመረና አካድኛን ይፋዊ ቋንቋ አደረገበት።
  • 2250 ገ. - የአካድ ንጉሥ ናራም-ሲን ስሜን ሶርያን ወርሮ በአሞራውያን ላይ ዘመተባቸው።
  • 2240 ገ. - የአካድ መንግሥት ተሰብሮ ኤላማዊው አገረ ገዡ ኩቲክ-ኢንሹሺናክ በአመጽ ተነሥቶ አገሩን ነጻ አወጣውና አካድኛን ተወ።
  • 2100 ገ. - የኡር ንጉሥ የኡር-ናሙ ሕገጋት ከተገኙት ሕገጋት ሁሉ ጥንታዊ ነው።
  • 2055-2047 ገ. - የኡር ንጉሥ አማር-ሲን ነገሠ።
  • 2030 ገ. - የኡር ንጉሥ ሹ-ሲን ሴት ልጁን ለአንሻን መስፍን በትዳር ሰጠ።
  • 2012 ገ. - በሺማሽኪ ንጉስ በኪንዳታ መሪነት ኤላማውያን ከሹሻን ሕዝብ ጋር ኡር ከተማን አጠፉና ንጉሣቸውን የሹ-ሲን ልጅ ኢቢ-ሲንን ማረኩት።
  • 1978 ገ. - የኤፓርቲ ሥርወ መንግሥት በኤላም ጀመረ።
  • 1900 ገ. - በል-ካፕ-ካፒአሦር ነገሠ።
  • 1850 ገ. - ከሹሻን ወደ ስሜን በሆነ ከተማ የነገሠ ኤላማዊ ንጉሥ ኩዱር-ማቡግ ልጁን ዋራድ-ሲንላርሳ ዙፋን ላይ አስቀመጠ።
  • 1820 ገ. - አሞራዊው ንጉሥ ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና።
  • 1800 ገ. - ቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈትዋዲ ኤል ሖል ግብጽ
  • 1770 ገ. - ሃሙራቢ ኤላማውያን አስወጥቶ የላርሳ ንጉሥ ሪም-ሲን ገለበጠውና ሜስጶጦምያን በሙሉ ገዛ።
  • 1603 ገ. - ኬጢያውያን ባቢሎንን አሸነፉ ካሳውያን በሜስጶጦምያ ተነሡ።
  • 1500 ገ. - ቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት በደብረ ሲና በኩል
  • 1500-1400 ገ. - የኪዳኑ ስርወ መንግሥት በኤላም
  • 1400-1210 ገ. - የኢጊሃልኪ ሥርወ መንግሥት በኤላም
  • 1370 ገ. ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ።
  • 1330 ገ. - የካሳውያን ንጉስ 2 ኩሪጋልዙ ለጊዜው ኤላምን ወረረ።
  • 1290 - የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ።
  • 1240 ገ. - ካሳዊ ንጉስ 4 ካሽቲሊያሽ ከኤላም ጋር ሲዋግ አላከናወነም።
  • 1232 - የኤላም ንጉሥ ኪዲን-ሑትራን የካሳውያን ንጉሥ ኤንሊል-ናዲን-ሹሚ አሸነፈ። * 1230 - የካሳውያን ንጉስ አዳድ-ሹማ-ኢዲና በኤላም ላይ አሸነፈ።
  • 1210-1100 - የሹትሩክ ሥርወ መንግስት በኤላም
  • 1184 - የኤላም ንጉሥ ሹትሩክ-ናሑንተ ከካሳውያንን ጋር ሲዋጋ የሃሙራቢ ሕገጋት የተጻፈበትን ድንጋይ ከመማረኩ በላይ የማርዱክና የማኒሽቱሹ ጣኦታትና የናራም-ሲን ሐውልት ወደ ሱስን ማረከባቸው።
  • 1190 ገ. - የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ወደቀ።
  • 1166 - የኤላም ንጉሥ ሹትሩክ-ናሑንተ ካሳውያንን በፍጹም ድል አደረጋቸው።
  • 1140 - የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በአሞራውያን አገር በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ።
  • 1130 - ሱስን ለባቢሎን ንጉሥ ለ1 ናቡከደነጾር ወደቀና የኤላም ንጉሥ ሑተሉሽ-ኢንሹሺናክ ወደ አንሻን ሸሸ።
  • 992-987 - የባቢሎን ንጉሥ ማር-ቢቲ-አፕላ-ኡሹር ነገሠ።
  • 920 - 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆኖ የአሦር ሃይል ታደሰ።
  • 890 - የአሦር ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹን ያስፋፋ ጀመር።
  • 865-831 - 3 ስልምናሶር በአሦር ነገሠ።
  • 831-819 - 5ኛ ሻምሺ-አዳድ በአሦር ነገሠ።
  • 818-790 - 3 አዳድ-ኒራሪ በአሦር ነገሠ።
  • 784 ገ. - አልያቴስልድያ ነገሠ።
  • 755 - አሦር በብሔራዊ ጦርነት ተይዞ ባቢሎን በንጉሱ ናቦፖላሣር መሪነት ነጻነቱን አዋጀ።
  • 754 - ፎሐ (ፑሉ) የሚባል አለቃ የአሦር መንግሥት ቀምቶ 3 ቴልጌልቴልፌልሶር ተብሎ ንጉስ ሆነ።
  • 751-725 - የኤላም ንጉሥ ሑምባኒጋሽ ነገሠ።
  • 748 - ቴልጌልቴልፌልሶር አርፋድን አጠፋ፤ ሐማትንም ያዘ።
  • 746 - ቴልጌልቴልፌልሶር ፊልሥጥኤምን ወርሮ የእስራኤልን ንጉስ ምናሔምን 1000 መክሊት ብር አስገበረ።
  • 740 - የእስራኤል ንጉስ ፋቁሔሶርያ (አራም) ንጉስ ረአሶን ጋራ አደጋ በይሁዳ ላይ ሲጣሉ የይሁዳ ንጉሥ አካዝ የመቅደሱን ወርቅ ሰጥቶ ከቴልጌልቴልፌልሶር እርዳታ ጠየቀ።
  • 737 - ቴልጌልቴልፌልሶር ወደ ባቢሎን ወርዶ ንጉሱን ናቡ-ሙኪን-ዜሪ ማረከና እራሱ 'የባቢሎን ንጉስ ፑሉ' ተብሎ ዘውዱን ተጫነ።
  • 735 - 5 ስልምናሶር በአሦር ነገሠ።
  • 733 - የእስራኤል ንጉሥ ሆሴዕ ግብርን ባቋረጠ ጊዜ የግብጽ ጠባቂነት አገኘ። ስለዚህ ስልምናሶር ወርሮ ከሦስት አመት ትግል በኋላ ሰማርያን ያዘና የእስራኤልን ቅሬታ ወደ ሌላ አገሮች ሰደዳቸው።
  • 730 - ስልምናሶር ሰማርያን እየከበባት ድንገት ከሞተ በኋላ ሻለቃው 2 ሳርጎን ዙፋኑን ያዘ።
  • 718 እና 716 - የኤላም ንጉሥ 2ኛ ሹትሩክ-ናሑንተ በ2ኛ ሳርጎን ሠራዊት እጅ ድል ሆነ።
  • 708 - የሳርጎን ልጅ ሰናክሬም መሮዳክ-ባላዳንን ገልብጦ የራሱን ልጅ አሹር-ናዲን-ሹሚ በባቢሎን ዙፋን ላይ ንጉስ አደረገው።
  • 702 - ሹትሩክ-ናሑንተ በወንድሙ ሐሉሹ ተገድሎ ይህ ሐሉሹ አሹር-ናዲን-ሹሚንና ባቢሎንን ማረከው።
  • 697 - ሰናክሬም ባቢሎንን አጠፋው።
  • 695-660 - ጉጌስ በልድያ ነገሠ።
  • 661 - የአስራዶን ልጅ አስናፈር ሱስንን ድል አድርጎ ወረራት።
  • 660 ገ. - መጀመርያ መሐለቅ በልድያ ተሠራ።
  • 660-629 - 2ኛ አርዲስ በልድያ ነገሠ።
  • 655 - የአሦር ንጉስ አስናፈር ሱሳን አጠፋ።
  • 648 - አስናፈር ኤላምን በሙሉ ሲያጠፋ እርሻቸውን በጨው ዘራ።
  • 629-618 ገ. - ሣድያቴስ በልድያ ነገሠ።
  • 628 - ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕገጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ።
  • 618-568 - 2ኛ አልያቴስ በልድያ ነገሠ።
  • 600 - የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ።
  • 595 - የባቢሎን ምርኮ - ይሁዳ በ2ኛ ናቡከደነጾር ተያዘ።
  • 593 - የሜዶን ንጉስ ኩዋክሻጥራ ልድያን ባጠቃ ግዜ፣ በአንድ ታላቅ ውግያ ግርዶሽ ድንገት መጥቶ ከዚያ ቀጥሎ በኪልቅያና በባቢሎን ነገሥታት አማካይነት ስምምነት ተደረገላቸውና ያንግዜ ሃሊስ ወንዝ የሜዶንና የልድያ ጠረፍ ሆነ።
  • 568-554 - ቅሮይሶስ በልድያ ነገሠ።
  • 554 - ቅሮይሶስ በፋርስ ንጉሥ በ2ኛ ቂሮስ እጅ ድል ስለ ሆኑ መንግሥቱ ወዲያው የፋርስ ክፍላገር ሆነ።
  • 546 - የፋርሶች አሐይመኒድ ነገሥታት ሱሳንን ያዙት።
  • 457 - ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት አወጡ።
  • 407 - ከአንድ ጨነፈር የተነሣ የሲቡላውያን መጻሕፍት ተማከሩና ሌክቲስቴርኒዩም የተባለው ሥነ ሥርዓት ለአማልክታቸው ጣኦት ተመሠረተ።
  • 375 - ለሲቡላውያን መጻሕፍት 10 ጠባቂዎች በሮማ ተሾሙ።
  • 350 ገ. - የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ።
  • 339 - የመቄዶን ንጉሥ ታላቁ እስክንድር ከፋርስ መንግሥት ጋር ሱሳን አሸነፈው።
  • 301 - ከሌላ ጨነፈር ቀጥሎ የሲቡላውያን መጻሕፍት ተማክረው መልሱ ጣኦቱን አይስኩላፒዩስ ወደ ሮማ ከኤፒዳውሮስ (በግሪክ) እንዲያመጡ ሆነ። ሆኖም የሮማ ሴናት በጦርነት ተይዞ ከአንድ ቀን ጸሎት በቀር ስለ አይስኩላፒዩስ ነገር ምንም አላደረገም።
  • 246 - 'የአበባ ጨዋታዎች' (Ludi Florales) በሲቡላውያን መጻሕፍት ምክር ተመሠረቱ።
  • 224 - የካርታጌና አለቃ ሃኒባል የሮማ ጭፍራ በካናይ ፍልሚያ ሲያጠፋ፥ መጻሕፍቱ ተማክረው እንደ ምክራቸው ሁለት ግሪኮችና ሁለት ጋውሎች በሮማ ገበያ በሕይወታቸው ተቀበሩ።
  • 214 - የሃን ሥርወ መንግሥትቻይና ተመሠረተ።
  • 212 - በካርታጌና ጦርነት ጊዜ የሮማ አበጋዝ ስኪፒዮ አፍሪካኑስ ከሲቡላውያን መጻሕፍት ምክር የተነሣ የኩቤሌ ጣኦት ከፔሢኖስ አምጥቶ አምልኮቷን በሮማ አስገባ።
  • 141 - ሮማውያን ሰርዴስን ገብተው ልድያ ወዲያው በሮማ መንግሥት ውስጥ የእስያ ጠቅላይ ግዛት ክፍል ሆነ።
  • 96-86 - የሱላ መሪነት በሮማ
  • 91 - የዩፒተር መቅደስ በሮማ ተቃጥሎ የሲቡላውያን መጻሕፍት ጠፉ።
  • 84 - የሮማ ላይኛ ምክር ቤት (ሴናት) ተልእኮዎች የሲቡል ትንቢቶች እንዲያገኙ ላኩዋቸው።
  • 71 - 'በሮማ ሦስት ቆርኔሌዎሶች ሊገዙ ነው' ከሚል ከአንዱ ትንቢት የተነሣ ፑብሊዩስ ቆርኔሌዎስ ሌንቱሉስ ሱራ አንድ ሤራ አደረገ።
  • 63 - 12 ፕቶለሜዎስ ወደ ግብጽ ዙፋን እንዲመለሱ ሮማውያን ሥራዊቱን መላካቸውን ሲማከሩ፣ መብራቅ በድንገት የዩፒተር ጣኦት መታ። ስለዚህ የሲቡል መጻሕፍቶች ተማክረው 'ከግብጽ አንድ ንጉሥ መቸም እርዳታ ቢለምንሽ፣ ወዳጅነትሽ አይቀርለት እንጂ ጣርና አደጋ እንዳያገኙሽ ሥራዊት ከቶ አትሥጪው' የሚል ትንቢት በመገኘቱ ይህ ቃል የፕቶሎሜዎስን መመለስ በጣም አቆየ።
  • 52 - 'በጳርቴ ላይ ማሸነፍ የቻለው ንጉሥ ብቻ ይሆናል' ስለሚል ትንቢት ቄሣር በሮማ ሬፑብሊክ ላይ ንጉሥነትን በቶሎ እንደሚይዝ ያለ ጭምጭምታ ተፈጠረ።

[ለማስተካከል] ዓመተ ምህረት


  • 108 - የሮማ ንጉስ ትራያኑስ ሱሳን ይዞ በአመጽ ምክንያት ቶሎ መመለስ ነበረበት። ይህም ሮማውያን ከሁሉ ወደ ምሥራቅ የደረሱበት ወቅት ነበረ።


  • 303 - የሮማ ንጉሥ ጋሌሪዎስ አልጋ ላይ ወድቆ ትንሽ ሊያርፍ ሲል በመንግሥቱ ግዛት ውስጥ ላሉት ክርስቲያኖች ሁሉ ይቅርታ ሰጠ።
  • 304 - ከሚልቪያን ድልድይ ፍልሚያ አስቀድሞ የተቃዋሚ አለቆች ማክሰንቲያስቈስጠንጢኖስ ሲያዘጋጁ ማክሰንቲያስ የሲቢሊንን መጻሕፍት አማከሩና ቈስጠንጢኖስ እምነታቸውን ከአፖሎ ወደ ክርስቶስ አዛወሩ። በፊልሚያውም የማክሰንቲያስ ድል መሆኑ ስመ ጥሩ ድርጊት ነው።
  • 305 - ሁለት የጋርዮሽ ቄሣሮች 1ኛ ቈስጠንጢኖስ እና ሊቂኒዎስ የሚላኖ አዋጅን አወጡ። ይህ ህግ ለሰው ሁሉ የሃይማኖት ነጻነት በማረጋገጥ የክርስቲያኖች መሬት ያለ ገደብ እንዲመልስላቸው የሚያዝዝ ነበር።
  • 317 - ቆንስጣንጢኖስ የኒቂያ ጉባኤ ጠሩ።
  • 353 - የሮማ ንጉሥ ዩሊያኖስ ከሐዲ መንግሥቱን ለጥቂት ግዜ ወደ ድሮ አረመኔ እምነት መለሠው።
  • 355 - የሮማ ንጉሥ ዩሊያኖስ ከሐዲ በጳርቴ ላይ ዘመቻ ሊያደርግ ሲል መጻሕፍቱን አማከረ። ከሮማ የደረሰውም መልስ በዛኛው አመት ጠረፍ መሻገሩን በግልጽ ደገፈው።
  • 372 - የካቶሊክ ቤተክርስቲያን በንጉሡ 1ኛ ቴዎዶስዮስ አዋጅ መሠረት የሮማ መንግስት ሃይማኖት በይፋ ተደረገ።
  • 397 - የአሪዮስ ክርስትና ትምህርት አራማጅ የሆነ ስቲሊኮ የሲቡላውያን መጻሕፍት በሮማ እንዳቃጠላቸው ይባላል።











  • 1400 - የቻይና ሰዎች ወርረው 'ዶንግ ዶ' (ሀኖይ)ን ይዘው ስሙን 'ዶንግ ጯን' አሉት።
  • 1420 - ዶንግ ጯን ወደ ቬትናም ሕዝብ ሲመለስ ስሙ 'ዶንግ ኪኝ' ሆነ።
  • 1431 - በአጼ ዘርዕ ያዕቆብ ዘመን አባ ጊዮርጊስ ከ1 ፈረንሳያዊ ጐባኝ ጋራ ስለ ሃይማኖት ስላነጋገሩ አንድ ተልእኮ ወደ ሮማ ተላከ።

[ለማስተካከል] 16ኛ ምዕተ ዓመት

[ለማስተካከል] 17ኛ ምዕተ ዓመት

[ለማስተካከል] 18ኛ ምዕተ ዓመት

[ለማስተካከል] 19ኛ ምዕተ ዓመት

ከምድር መንቀጥቀጥ በሳውስ ካሮላይና 100 ሰዎች ሞቱ።