ታው

ከውክፔዲያ

ተ ቱ ቲ ታ ቴ ት ቶ ቷ



አቡጊዳ ታሪክ

ታው (ወይም ታዊ) በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ 22ኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥሶርያም ፊደሎች 22ኛው ፊደል "ታው" ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል "ታእ" ተብሎ በ"አብጃድ" ተራ 22ኛ ነው።

አማርኛ ደግሞ "ቸ ቹ ቺ ቻ ቼ ች ቾ" ከ"ተ..." ትንሽ ተቀይሯል።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል ቅድመ-ሴማዊ ሣባ ግዕዝ
Z9


የታው መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የመስቀል ስዕል መስለ። ይህን የመሰለው ሃይሮግሊፍጥንታዊ ግብጽኛ "ሰውእ" ነበር።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
ታው ታው ת ታው


የከነዓን "ታው" እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ ታው የአረብኛም "ታእ" ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት "ታው" (Τ, τ) አባት ሆነ። እሱም የላቲን አልፋቤት (T t) እና የቂርሎስ አልፋቤት (Т т) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ"ታው" ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል።