አሙ አሆተፕሬ

ከውክፔዲያ
አሙ አሆተፕሬ
የአሆተፕሬ ስም በጢንዚዛ ዕንቁ ላይ እንደ ተጻፈ
የአሆተፕሬ ስም በጢንዚዛ ዕንቁ ላይ እንደ ተጻፈ
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1791-1786 ዓክልበ. ግ.
ቀዳሚ ቃረህ ኻዎሰሬ
ተከታይ ሸሺ ማዓይብሬ
ሥርወ-መንግሥት 14ኛው ሥርወ መንግሥት


አሙ አሆተፕሬ ግብጽን በ፪ኛው ጨለማ ዘመን (14ኛው ሥርወ መንግሥት) ምናልባት ከ1791 እስከ 1786 ዓክልበ. ግድም ድረስ የገዛ ፈርዖን ነበረ።

የግብጽ ታሪክ ሊቅ ኪም ራይሆልትሥነ ቅርስ እንደሚያስረዳው፣ ከቃረህ ኻዎሰሬ ቀጥሎ አሙ አሆተፕሬ በአባይ ወንዝ አፍ ዙሪያ ለጤቤስ ፈርዖኖች ተገዥ ሆኖ ነገሠ። ሕዝቡ ከከነዓን የደረሱ ሴማዊ እረኞችና ነጋዴዎች ነበሩ።

አያሌ (60 ያህል) የ«አሙ» ወይም የ«አሆተፕሬ» ጢንዚዞች በዚያ ወቅት በዙሪያው እንደ ገዛ ይገልጻሉ፤ እነዚህም ስያሜዎች አብረው ባይታዩም ለአንዱ ፈርዖን መሆናቸው ይታስባል። ከነዚህ ቅርሶች ጥቂቶች በከነዓን፣ በአቢዶስ ወይም በኩሽ መንግሥት (ሰምና) በመገኘታቸው የንግድ ተቀባዮቹን ያመልክታል።[1] ሆኖም በአንዳንድ ሊቃውንት አስተሳሰብ ዘንድ፣ አሆተፕሬ በኋላ በ16ኛው ሥርወ መንግሥት ውስጥ ነበር የነገሠ።


ቀዳሚው
(ቃረህ ኻዎሰሬ)
አባይ ወንዝ አፍ (ጌሤም) ፈርዖን
1791-1786 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ሸሺ ማዓይብሬ
  1. ^ Kim Ryholt, 1997, The Political Situation in Egypt During the Second Intermediate Period p. 365.