አማራ (ክልል)

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አማራ ክልል

አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ነው። ዋና ከተማ ባሕር-ዳር ነው። 156,960 ካሬ ኪ.ሜ. የሚሆን የቦታ ስፋት ሲኖረው የሕዝብ ብዛት ደግሞ (በ1991) 19,120,005 ነው። ክልሉ አራት ዞኖች ሲኖሩት፣ እነርሱም፤

በዚሁ ክልል ውስጥ ሰሜን ሸዋ አንዱ የአማራ ክልል እና ባለታሪክ ክልል ሲሆን የአጼ ሚኒሊክ የትውልድ ሀገር ከደብረብርሃን 5 ኪሎሜትር ርቀት አንጎለላ አካባቢ ሲሆን ይህ ክልል በጀግንነት የሚታወቅ ቦታ ነው። ከእነሱም ውስጥ ተጉለትቡልጋምንጃርጅሩመሬ/መርሀቤቴ/ ፣ መንዝይፋትአንኮበር ፣እና ሌሎችም አሉ። ይሄ ዞን ጀግንነት ብቻ ሳይሆን ደግነትና እንግዳ ተቀባይ ፣ አክባሪ ፣ ሀይማኖተኛ ፣ፈሪሀ እግዚአብሔር በልቡ ውስጥ ያለው ፣ አትንኩኝ ባይ ፣ ጀግና ሕዝብ ነው። ይህ ክልል 98.5 በመቶ አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ነው ። ነገር ግን ጥንቱ የ ቤተ አምሐራ ምድር መነሻ የ አሁኑን ወሎ አጠቃሎ የያዘ ሲሆን በውስጡም ጥንታዊውን አምሐራ ሳይንት፣ ደብረሲና፣ ተንታ፣ወግዲ፣ከለላ፣ለጋንቦ፣ኩታበር፣አምባሰል፣ሮሃ(ላሊበላ)፣ደላንት ና ዳውንት፣ግዳን...ወዘተ ያጠቃልላል።

በአማራ ክልል ዉስጥ 11 ዞኖች ሲገኙ ከነዚህ ዉስጥ ሰሜን ጎንደር አንዱ ነው። ዞኑ ከ20 በላይ ወረዳዎች ሲኖሩት ብዙ ታሪካዊ ቦታዎች ይገኛሉ። ከነዚህም መካከል የፋሲል ግንብየሲስኒዮስ በተ መንግስትየዞዝ አምባ ውቅር ፍልፍል ገዳም፣ ዋሻ ፣ የጎርጎራ ወደብየወርቃምባ ውቅር ፍልፍል በተ ጊዎርጊስ ገዳም... የራስ ዳሸን ተራራ ወዘተ. ናቸዉ።

ምዕ/ጎጃም ዞንም በዚሁ ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በውስጡ ቡሬ ወምበርማ ወረዳ፡ ሰከላ፡ ይልማና ደንሳ፡ ደምበጫዳሞት ወረዳዎችን ይገኙበታል። ቡሬ ወረዳ የንግድ ማኣከል ስትሆን ወለጋን (ነቀምትን)፡ አዲስ አበባን አና ባህር ዳርን ታገናኛለች። በወረዳዋ ዉስጥ ሁሉም አዝዕርቶች የሚመረቱ ቢሆንም በዋናነት በርበሬጤፍበቆሎ፡ በብዛት ይመረታሉ። ቡሬ ወረዳ አንድ ግብርና ማሰልጠኛ፡ አንድ ሀይስኩል፡ 1 ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ፡ 1 ፕሪፓራቶሪ አና 3 አንደኛና መለስተኛ ት/ቤቶች ይገኙባታል። የማዕድን ዉሃ ፋብሪካና ሌሎች የግብርና ማቀነባበሪያዎችም ይገኛሉ። ለግብርና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ የአየር ንብረትና መሬት ያላት ወረዳ ስትሆን ባለሃብቶች በዚህ አካባቢ ቢሰማሩ ዕራሳቸዉን ጠቅመቅው ህብረተሰቡን መጥቀም ይችላሉ።

በመስህብ ደረጃ በአካባቢዉ ብዙ ታሪካዊ ገዳማትና ለቱሪስት መስህብ ኢሂኑ ሚችሉ ቦታዎች ቢኖሩም ብዙም የታወቁና ለቱሪስት የተዋወቁ አይደሉም። ለምሳሌ ፦ አደል ሚካዒል፡ ይስር ፋፋቴ፡ ባንጃ ተራራው ወዘተ...


ኢትዮጵያ

ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ
አስተዳደራዊ ክልሎች - ትግራይ | አፋር | አማራ | ኦሮሚያ | ሶማሌ | ቤንሻንጉል-ጉምዝ | ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች | ጋምቤላ | ሐረሪ | አዲስ አበባ | ድሬዳዋ
ቋንቋዎች - አማርኛ | ግዕዝ | ኦሮምኛ | ትግርኛ | ጉራጊኛ | ሶማሊኛ | አፋርኛ | ሲዳምኛ | ሃዲያኛ | ከምባትኛ | ወላይትኛ | ጋሞኛ | ከፋኛ | ሃመርኛ | ስልጢኛ | ሀደሪኛ
መልክዓ-ምድር - አባይ | አዋሽ | ራስ-ዳሽን | ሶፍ-ዑመር | ጣና | ደንከል | ላንጋኖ | አቢያታ | ሻላ
ከተሞች - የኢትዮጵያ ከተሞች

የኔ መሣርያዎች

Variants
Actions
የማውጫ ቁልፎች
ጠቃሚ መሣሪያዎች
በሌሎች ቋንቋዎች