አማራ (ክልል)
አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ነው። ዋና ከተማ ባሕር-ዳር ነው። 156,960 ካሬ ኪ.ሜ. የሚሆን የቦታ ስፋት ሲኖረው የሕዝብ ብዛት ደግሞ (በ1991) 19,120,005 ነው። ክልሉ አራት ዞኖች ሲኖሩት፣ እነርሱም፤
በዚሁ ክልል ውስጥ ሰሜን ሸዋ አንዱ የአማራ ክልል እና ባለታሪክ ክልል ሲሆን የአጼ ሚኒሊክ የትውልድ ሀገር ከደብረብርሃን 5 ኪሎሜትር ርቀት አንጎለላ አካባቢ ሲሆን ይህ ክልል በጀግንነት የሚታወቅ ቦታ ነው። ከእነሱም ውስጥ ተጉለት ፣ቡልጋ ፣ ምንጃር ፣ ጅሩ ፣መሬ/መርሀቤቴ/ ፣ መንዝ ፣ ይፋት ፣ አንኮበር ፣እና ሌሎችም አሉ። ይሄ ዞን ጀግንነት ብቻ ሳይሆን ደግነትና እንግዳ ተቀባይ ፣ አክባሪ ፣ ሀይማኖተኛ ፣ፈሪሀ እግዚአብሔር በልቡ ውስጥ ያለው ፣ አትንኩኝ ባይ ፣ ጀግና ሕዝብ ነው። ይህ ክልል 98.5 በመቶ አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ነው ። ነገር ግን ጥንቱ የ ቤተ አምሐራ ምድር መነሻ የ አሁኑን ወሎ አጠቃሎ የያዘ ሲሆን በውስጡም ጥንታዊውን አምሐራ ሳይንት፣ ደብረሲና፣ ተንታ፣ወግዲ፣ከለላ፣ለጋንቦ፣ኩታበር፣አምባሰል፣ሮሃ(ላሊበላ)፣ደላንት ና ዳውንት፣ግዳን...ወዘተ ያጠቃልላል።
በአማራ ክልል ዉስጥ 11 ዞኖች ሲገኙ ከነዚህ ዉስጥ ሰሜን ጎንደር አንዱ ነው። ዞኑ ከ20 በላይ ወረዳዎች ሲኖሩት ብዙ ታሪካዊ ቦታዎች ይገኛሉ። ከነዚህም መካከል የፋሲል ግንብ ፣የሲስኒዮስ በተ መንግስት፣ የዞዝ አምባ ውቅር ፍልፍል ገዳም፣ ዋሻ ፣ የጎርጎራ ወደብ፣ የወርቃምባ ውቅር ፍልፍል በተ ጊዎርጊስ ገዳም... የራስ ዳሸን ተራራ ወዘተ. ናቸዉ።
ምዕ/ጎጃም ዞንም በዚሁ ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በውስጡ ቡሬ ወምበርማ ወረዳ፡ ሰከላ፡ ይልማና ደንሳ፡ ደምበጫና ዳሞት ወረዳዎችን ይገኙበታል። ቡሬ ወረዳ የንግድ ማኣከል ስትሆን ወለጋን (ነቀምትን)፡ አዲስ አበባን አና ባህር ዳርን ታገናኛለች። በወረዳዋ ዉስጥ ሁሉም አዝዕርቶች የሚመረቱ ቢሆንም በዋናነት በርበሬ፡ ጤፍ፡ በቆሎ፡ በብዛት ይመረታሉ። ቡሬ ወረዳ አንድ ግብርና ማሰልጠኛ፡ አንድ ሀይስኩል፡ 1 ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ፡ 1 ፕሪፓራቶሪ አና 3 አንደኛና መለስተኛ ት/ቤቶች ይገኙባታል። የማዕድን ዉሃ ፋብሪካና ሌሎች የግብርና ማቀነባበሪያዎችም ይገኛሉ። ለግብርና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ የአየር ንብረትና መሬት ያላት ወረዳ ስትሆን ባለሃብቶች በዚህ አካባቢ ቢሰማሩ ዕራሳቸዉን ጠቅመቅው ህብረተሰቡን መጥቀም ይችላሉ።
በመስህብ ደረጃ በአካባቢዉ ብዙ ታሪካዊ ገዳማትና ለቱሪስት መስህብ ኢሂኑ ሚችሉ ቦታዎች ቢኖሩም ብዙም የታወቁና ለቱሪስት የተዋወቁ አይደሉም። ለምሳሌ ፦ አደል ሚካዒል፡ ይስር ፋፋቴ፡ ባንጃ ተራራው ወዘተ...
| ኢትዮጵያ |
|
ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ |
| ጅምር! (ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። እርስዎ ሊያስፋፉት ይችላሉ!) |