አራም (የሴም ልጅ)

ከWikipedia

ዘልለው ለመሐድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አራም ሴም (ዕብራይስጥאֲרָם) በመጽሐፍ ቅዱስ ኦሪት ዘፍጥረት (ምዕ. 10) መሠረት የኖህ ልጅ ሴም ከወለዱት ልጆች አንድ ሲሆን የዑፅሁልጌቴርሞሶሕ አባት ይባላል።

በጥንቱ ታሪከኞች ዘንድ፣ የስሜን ሜስጶጦምያና የሶርያ ሕዝብ የአራማውያን አባት እሱ ነበር። የአራም ሕዝብ ከ1300 ዓክልበ. ጀምሮ በእርግጥ ሲታወቅ፣ በ2300 ዓክልበ. በአካድ ንጉሥ ሳርጎን በተወራ ዘመቻ ግን «አራም» የሚባል አገር ይመዘገባል።

መጽሐፈ ኩፋሌ (9፡19) መሠረት፣ የኖህ ልጆች ምድሪቱን ሲያከፋፈሉ የአራም ልጆች የወረሱት ርስት ከኤፍራጥስና ከጤግሮስ ወንዞች መካከል ያለው አገር ሁሉ ያጠቅልል ነበር። ይሁንና በታሪካዊው ዘመን አራማውያን ይህን አገር በሙሉ ሠፍረው አያውቁም።

በብሉይ ኪዳን የተጠቀሰው ካራንንም ከተማ የጠቀለለው ሀገር «አራም-ናሐራይን» (የሁለት ወንዞች አራም) እንዲሁም በአካባቢው የተገኙት አራም-ደማስቆአራም-ረሆብ በአራም ልጆች እንደ ተመሰረቱ ይታመናል።

ደግሞ የሴም ልጅ አራም በማንዳያውያን ሃይማኖት እንደ ነቢይ ሆኖ ይከብራል።

የኔ መሣርያዎች