አስርቱ ቃላት
ከውክፔዲያ
አስርቱ ቃላት ወይም አስርቱ ትዕዛዛት በመጽሐፍ ቅዱስ ዘንድ እግዚአብሔር ለሙሴ በደብረ ሲና የገለጣቸው 10 ትዕዛዛት ወይም ሕግጋት ናቸው። የሚገኘው በኦሪት ዘጸአት 20፡2-17 ሲሆን፣ ዳግመኛ በኦሪት ዘዳግም 5፡6-21 በጥቃቅን ተለውጦ ሊታዩ ይችላሉ። እስከምናውቀው ድረስ፣ መጀመርያ የተጻፉበት ቋንቋ ዕብራይስጥ ነበረ።
ማውጫ |
[ለማስተካከል] ፩ (ዘጸአት 20፡2-3፣ ዘዳግም 5፡6-7)
- «አኖኪ ይሆዋህ ኤሎሄይካ እሼር ሆጸእቲካ መኤሬጽ ሚጽረዪም ሚበይት ዕባዲም።»
- «ሎእ-ዪህዬህ ልካ ኤሎሂም እሐሪም ዐል-ፓናየ።»
አማርኛ፦
[ለማስተካከል] ፪ (ዘጸአት 20፡4-6፤ ዘዳግም 5፡8-10)
ዕብራይስጥ፦
- «ሎእ-ተዕሤህ ልካ ፌሴል፣ ውካል-ቲሙናህ እሼር በሻመዪም ሚመዐል፣ ወእሼር ባአሬጽ ሚታሐት፣ ወእሼር በመዪም ሚተሐት ላአሬጽ።»
- «ሎእ-ቲሽተሕዌህ ላሄም፣ ውሎእ ታዓብደም፣ ኪ አኖኪ ይሆዋህ ኤሎሄይካ ኤል ቀናእ፣ ፎቀድ ዕዎን አቦት ዐል-ባኒም ዐል-ሺለሺም ውዐል-ሪበዒም ልሥንአይ፤
- ውዖሤህ ሔሜድ ለእላፊም ልኦህበይ ኡልሾምረይ ሚጽዎታይ።»
አማርኛ፦
- በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ።
- አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም፤ በሚጠሉኝ እስከ ሦስተኛና እስከ አራተኛ ትውልድ ድረስ የአባቶችን ኃጢአት በልጆች ላይ የማመጣ፤
- ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና።
[ለማስተካከል] ፫ (ዘጸአት 20፡7፤ ዘዳግም 5፡11)
ዕብራይስጥ፦
- «ሎእ ቲሣእ ኤት-ሸም-ይሆዋህ ኤሎሄይካ ለሻውእ፤ ኪ ሎእ ይነቄህ ይሆዋህ ኤት እሼር-ዪሣእ ኤት ሽሞ ለሻውእ።»
አማርኛ፦
- የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና።
[ለማስተካከል] ፬ (ዘጸአት 20፡8-11፤ ዘዳግም 5፡12-15)
ዕብራይስጥ፦
- «ዛኮር ኤት-ዮም ሀሸባት ልቀድሾ።»
- «ሸሼት ያሚም ተዕቦድ፣ ውዓሢታ ካል-ምለእክቴካ፤
- ውዮም ሀሽቢዒ ሸባት ለይሆዋህ ኤሎሄይካ፤ ሎእ-ተዕሤህ ካል-ምላእካህ፣ አታህ፣ ኡቢንካ፣ ኡቢቴካ፤ ዐብድካ፣ ወእማትካ፣ ኡብሄምቴካ፣ ውገርካ እሼር ቢሽዓሬይካ።»
- «ኪ ሸሼት-ያሚም ዓሣህ ይሆዋህ ኤት-ሀሻመዪም ውኤት-ሀአሬጽ፣ ኤት-ሀያም፣ ውኤት-ካል-እሼር-ባም፤ ወያነሕ በዮም ሀሽቢዒ፤ ዐል-ከን በረክ ይሆዋህ ኤት-ዮም ሀሸባት ወይቀድሸሁ።»
አማርኛ*፦
- የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ።
- ስድስት ቀን ሥራ፣ ተግባርህንም ሁሉ አድርግ፤
- ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ፥ ወንድ ልጅህም፥ ሴት ልጅህም፥ ሎሌህም፥ ገረድህም፥ ከብትህም፥ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ፤
- እግዚአብሔር በስድስት ቀን ሰማይንና ምድርን፥ ባሕርንም፥ ያለባቸውንም ሁሉ ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን ዐርፎአልና፤ ስለዚህ እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታልም።
- *(በኦሪት ዘዳግም 5፡12-15፣ ቃሉ እንዲህ ሲል ከኦሪት ዘጸአት 20፡8-11 ትንሽ ይለያል፦ «የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ ጠብቅ። ስድስት ቀን ሥራ፣ ተግባርህንም ሁሉ አድርግ፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ እንደምታርፍ ሎሌህና ገረድህ ያርፉ ዘንድ፥ አንተ ወንድ ልጅህም ሴት ልጅህም ሎሌህም ገረድህም በሬህም አህያህም ከብትህም ሁሉ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ። አንተም በግብፅ ባሪያ እንደ ነበርህ አስብ፣ እግዚአብሔር አምላክህ በጸናች እጅና በተዘረጋ ክንድ ከዚያ አወጣህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ የሰንበትን ቀን ትጠብቅ ዘንድ አዘዘህ።»)
[ለማስተካከል] ፭ (ዘጸአት 20፡12፤ ዘዳግም 5፡16)
ዕብራይስጥ፦
- «ከበድ ኤት-አቢካ ውኤት-ኢሜካ፤ ልመዐን የእሪኩን ያሜይካ ዐል ሃእዳማህ እሼር-ይሆዋህ ኤሎሄይካ ኖተን ልካ።»
አማርኛ፦
- *(በኦሪት ዘዳግም 5፡16፣ «መልካምም እንዲሆንልህ» የሚለውን ይጨመራል።)
[ለማስተካከል] ፮ (ዘጸአት 20፡13፤ ዘዳግም 5፡17)
ዕብራይስጥ፦
- «ሎእ ቲርጸሐ።»
አማርኛ፦
- አትግደል።
[ለማስተካከል] ፯ (ዘጸአት 20፡14፤ ዘዳግም 5፡18)
ዕብራይስጥ፦
- «ሎእ ቲንአፍ።»
አማርኛ፦
- አታመንዝር።
[ለማስተካከል] ፰ (ዘጸአት 20፡15፤ ዘዳግም 5፡19)
ዕብራይስጥ፦
- «ሎእ ቲግኖብ።»
አማርኛ፦
- አትስረቅ።
[ለማስተካከል] ፱ (ዘጸአት 20፡16፤ ዘዳግም 5፡20)
ዕብራይስጥ፦
- «ሎእ-ቴዕኔህ ብረዕካ ዐድ ሻቄር።»
አማርኛ፦
- በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር።
[ለማስተካከል] ፲ (ዘጸአት 20፡17፤ ዘዳግም 5፡21)
ዕብራይስጥ፦
- «ሎእ ተሕሞድ በይት ረዔካ፤ ሎእ ተሕሞድ ኤሼት ረዔካ፣ ውአብዶ፣ ወእማቶ፣ ውሾሮ፣ ወሕሞሮ፣ ውኮል እሼር ልረዔካ።»
አማርኛ፦
- *(በኦሪት ዘዳግም 5፡21፣ ቃሉ እንዲህ ሲል ከኦሪት ዘጸአት 20፡17 ትንሽ ይለያል፦ «የባልንጀራህን ሚስት አትመኝ፤ የባልንጀራህንም ቤት እርሻውንም ሎሌውንም ገረዱንም በሬውንም አህያውንም፥ ከባልንጀራህ ገንዘብ ሁሉ ማናቸውንም አትመኝ።)