አስርቱ ቃላት

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አስርቱ ቃላት ወይም አስርቱ ትዕዛዛትመጽሐፍ ቅዱስ ዘንድ እግዚአብሔርሙሴደብረ ሲና የገለጣቸው 10 ትዕዛዛት ወይም ሕግጋት ናቸው። የሚገኘው በኦሪት ዘጸአት 20፡2-17 ሲሆን፣ ዳግመኛ በኦሪት ዘዳግም 5፡6-21 በጥቃቅን ተለውጦ ሊታዩ ይችላሉ። እስከምናውቀው ድረስ፣ መጀመርያ የተጻፉበት ቋንቋ ዕብራይስጥ ነበረ።

ማውጫ

፩ (ዘጸአት 20፡2-3፣ ዘዳግም 5፡6-7)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ (በፊደል)፦

  • «አኖኪ ይሆዋህ ኤሎሄይካ እሼር ሆጸእቲካ መኤሬጽ ሚጽረዪም ሚበይት ዕባዲም።»
  • «ሎእ-ዪህዬህ ልካ ኤሎሂም እሐሪም ዐል-ፓናየ።»

አማርኛ

፪ (ዘጸአት 20፡4-6፤ ዘዳግም 5፡8-10)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ሎእ-ተዕሤህ ልካ ፌሴል፣ ውካል-ቲሙናህ እሼር በሻመዪም ሚመዐል፣ ወእሼር ባአሬጽ ሚታሐት፣ ወእሼር በመዪም ሚተሐት ላአሬጽ።»
  • «ሎእ-ቲሽተሕዌህ ላሄም፣ ውሎእ ታዓብደም፣ ኪ አኖኪ ይሆዋህ ኤሎሄይካ ኤል ቀናእ፣ ፎቀድ ዕዎን አቦት ዐል-ባኒም ዐል-ሺለሺም ውዐል-ሪበዒም ልሥንአይ፤
  • ውዖሤህ ሔሜድ ለእላፊም ልኦህበይ ኡልሾምረይ ሚጽዎታይ።»

አማርኛ

  • በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ።
  • አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም፤ በሚጠሉኝ እስከ ሦስተኛና እስከ አራተኛ ትውልድ ድረስ የአባቶችን ኃጢአት በልጆች ላይ የማመጣ፤
  • ለሚወድዱኝ፥ ትእዛዜንም ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን የማደርግ እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና።

፫ (ዘጸአት 20፡7፤ ዘዳግም 5፡11)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ሎእ ቲሣእ ኤት-ሸም-ይሆዋህ ኤሎሄይካ ለሻውእ፤ ኪ ሎእ ይነቄህ ይሆዋህ ኤት እሼር-ዪሣእ ኤት ሽሞ ለሻውእ።»

አማርኛ

  • የእግዚአብሔርን የአምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ፤ እግዚአብሔር ስሙን በከንቱ የሚጠራውን ከበደል አያነጻውምና።

፬ (ዘጸአት 20፡8-11፤ ዘዳግም 5፡12-15)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ዛኮር ኤት-ዮም ሀሸባት ልቀድሾ።»
  • «ሸሼት ያሚም ተዕቦድ፣ ውዓሢታ ካል-ምለእክቴካ፤
  • ውዮም ሀሽቢዒ ሸባት ለይሆዋህ ኤሎሄይካ፤ ሎእ-ተዕሤህ ካል-ምላእካህ፣ አታህ፣ ኡቢንካ፣ ኡቢቴካ፤ ዐብድካ፣ ወእማትካ፣ ኡብሄምቴካ፣ ውገርካ እሼር ቢሽዓሬይካ።»
  • «ኪ ሸሼት-ያሚም ዓሣህ ይሆዋህ ኤት-ሀሻመዪም ውኤት-ሀአሬጽ፣ ኤት-ሀያም፣ ውኤት-ካል-እሼር-ባም፤ ወያነሕ በዮም ሀሽቢዒ፤ ዐል-ከን በረክ ይሆዋህ ኤት-ዮም ሀሸባት ወይቀድሸሁ።»

አማርኛ*፦

  • ሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ።
  • ስድስት ቀን ሥራ፣ ተግባርህንም ሁሉ አድርግ፤
  • ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ፥ ወንድ ልጅህም፥ ሴት ልጅህም፥ ሎሌህም፥ ገረድህም፥ ከብትህም፥ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ፤
  • እግዚአብሔር በስድስት ቀን ሰማይንና ምድርን፥ ባሕርንም፥ ያለባቸውንም ሁሉ ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን ዐርፎአልና፤ ስለዚህ እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታልም።



*(በኦሪት ዘዳግም 5፡12-15፣ ቃሉ እንዲህ ሲል ከኦሪት ዘጸአት 20፡8-11 ትንሽ ይለያል፦ «የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ ጠብቅ። ስድስት ቀን ሥራ፣ ተግባርህንም ሁሉ አድርግ፤ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ አንተ እንደምታርፍ ሎሌህና ገረድህ ያርፉ ዘንድ፥ አንተ ወንድ ልጅህም ሴት ልጅህም ሎሌህም ገረድህም በሬህም አህያህም ከብትህም ሁሉ በደጆችህም ውስጥ ያለ እንግዳ በእርሱ ምንም ሥራ አትሥሩ። አንተም በግብፅ ባሪያ እንደ ነበርህ አስብ፣ እግዚአብሔር አምላክህ በጸናች እጅና በተዘረጋ ክንድ ከዚያ አወጣህ፤ ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ የሰንበትን ቀን ትጠብቅ ዘንድ አዘዘህ።»)

፭ (ዘጸአት 20፡12፤ ዘዳግም 5፡16)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ከበድ ኤት-አቢካ ውኤት-ኢሜካ፤ ልመዐን የእሪኩን ያሜይካ ዐል ሃእዳማህ እሼር-ይሆዋህ ኤሎሄይካ ኖተን ልካ።»

አማርኛ

  • አባትህንና እናትህን አክብር፤ እግዚአብሔር አምላክህ በሚሰጥህ ምድር ዕድሜህ እንዲረዝም*።


*(በኦሪት ዘዳግም 5፡16፣ «መልካምም እንዲሆንልህ» የሚለውን ይጨመራል።)

፮ (ዘጸአት 20፡13፤ ዘዳግም 5፡17)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ሎእ ቲርጸሐ።»

አማርኛ

  • አትግደል።

፯ (ዘጸአት 20፡14፤ ዘዳግም 5፡18)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ሎእ ቲንአፍ።»

አማርኛ

  • አታመንዝር።

፰ (ዘጸአት 20፡15፤ ዘዳግም 5፡19)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ሎእ ቲግኖብ።»

አማርኛ

  • አትስረቅ።

፱ (ዘጸአት 20፡16፤ ዘዳግም 5፡20)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ሎእ-ቴዕኔህ ብረዕካ ዐድ ሻቄር።»

አማርኛ

  • በባልንጀራህ ላይ በሐሰት አትመስክር።

፲ (ዘጸአት 20፡17፤ ዘዳግም 5፡21)[ለማስተካከል]

ዕብራይስጥ

  • «ሎእ ተሕሞድ በይት ረዔካ፤ ሎእ ተሕሞድ ኤሼት ረዔካ፣ ውአብዶ፣ ወእማቶ፣ ውሾሮ፣ ወሕሞሮ፣ ውኮል እሼር ልረዔካ።»

አማርኛ

  • የባልንጀራህን ቤት አትመኝ፤ የባልንጀራህን ሚስት ሎሌውንም ገረዱንም በሬውንም አህያውንም ከባልንጀራህ ገንዘብ ሁሉ ማናቸውንም አትመኝ።


*(በኦሪት ዘዳግም 5፡21፣ ቃሉ እንዲህ ሲል ከኦሪት ዘጸአት 20፡17 ትንሽ ይለያል፦ «የባልንጀራህን ሚስት አትመኝ፤ የባልንጀራህንም ቤት እርሻውንም ሎሌውንም ገረዱንም በሬውንም አህያውንም፥ ከባልንጀራህ ገንዘብ ሁሉ ማናቸውንም አትመኝ።)