አሹር-ዱጉል
አሹር-ዱጉል ከ1678 እስከ 1672 ዓክልበ. ('ኡልትራ አጭሩ' አቆጣጠር) የአሦር ንጉሥ ነበረ።
የአሦር ነገሥታት ዝርዝር የተባለው ሰነድ እንደሚለው፣ ለ፮ ዓመታት ከ1 እሽመ-ዳጋን ቀጥሎ ነገሠ። ስለ አሹር ዱጉል በተጨማሪ እንዲህ ይተርካል፦ «አሹር-ዱጉል ዲቃላ ልጅ ነበረ፣ የዙፋን ማዕረግ አልነበረውም። በአሹር-ዱጉል ዘመን መጀመርያ፣ 6 ሌሎች «ዲቃላ» የተባሉ ጣውንት ነገሥታት ተነሡ፦ አሹር-አፕላ-ኢዲ፣ ናሲር-ሲን፣ ሲን-ናሚር፣ ኢፕቂ-ኢሽታር፣ አዳድ-ሳሉሉ እና አዳሲ ናቸው።»
ከነዚህ ስድስት በላይ፣ በሌላ መዝገብ ዘንድ ሁለት ሌሎች፣ ሙት-አሽኩር (የእሽመ-ዳጋን ልጅ)፣ እና ሪሙ-... ከእሽመ-ዳጋን በኋላ ይዘርዝራል እንጂ ሌሎቹን አይጠቅስም። ከዚህ በላይ በዚህ ወቅት የባቢሎን (የሃሙራቢ) አገረ ገዥ ፑዙር-ሲን ንጉሡን አሲኑም (የሻምሺ-አዳድ ልጅ-ልጅ) አሞራዊ ስለ ነበር ከዙፋኑ እንዳባረረው በማለት አስቀረጸ። ስለዚህ በተጠቅላላ በነዚህ ፮ ዓመታት ምናልባት ፲ ሰዎች ለአሦር ዙፋን ይወዳደሩ ነበር።
የአሹር-ዱጉል ተከታይ በዝርዝሩ ላይ የተጠቀሰው አዳሲ ልጅ ቤሉ-ባኒ ይባላል። ስለዚህ ያ አዳሲ እንደ አዲሱ አሦራዊ ሥርወ መንግሥት መስራች ይቆጠራል።
የዓመት ስሞች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
የያንዳንዱ አሦራዊ ዓመት ስም ለዚያ ዓመት የተሾመው የሊሙ ስም ነበረ። ከዚህ በታች የዓመቱ ሊሙ እና የሊሙ አባት ስም እንደ ኡልትራ አጭር አቆጣጠር ይዘርዝራሉ።[1]
- 1678 ዓክልበ. - አሁ-ዋቃር
- 1677 ዓክልበ. - ኪዙሩም
- 1676 ዓክልበ. - ዳዲያ
- 1675 ዓክልበ. - ያማሃያ
- 1674 ዓክልበ. - አዳድ-ባኒ
- 1673 ዓክልበ. - ኤናም-አሹር፣ አሹር-ታክላኩ ልጅ
- 1672 ዓክልበ. - አታያ፣ ሻማያ ልጅ
ቀዳሚው 1 እሽመ-ዳጋን |
የአሦር ንጉሥ 1678-1672 ዓክልበ. ግድም |
ተከታይ ቤሉ-ባኒ |
ዋቢ መጽሐፍት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ^ የመስጴጦምያ ነገሥታት (ፈረንሳይኛ)