አሹር-ዱጉል

ከውክፔዲያ

አሹር-ዱጉል ከ1678 እስከ 1672 ዓክልበ. ('ኡልትራ አጭሩ' አቆጣጠር) የአሦር ንጉሥ ነበረ።

የአሦር ነገሥታት ዝርዝር የተባለው ሰነድ እንደሚለው፣ ለ፮ ዓመታት ከ1 እሽመ-ዳጋን ቀጥሎ ነገሠ። ስለ አሹር ዱጉል በተጨማሪ እንዲህ ይተርካል፦ «አሹር-ዱጉል ዲቃላ ልጅ ነበረ፣ የዙፋን ማዕረግ አልነበረውም። በአሹር-ዱጉል ዘመን መጀመርያ፣ 6 ሌሎች «ዲቃላ» የተባሉ ጣውንት ነገሥታት ተነሡ፦ አሹር-አፕላ-ኢዲ፣ ናሲር-ሲን፣ ሲን-ናሚር፣ ኢፕቂ-ኢሽታር፣ አዳድ-ሳሉሉ እና አዳሲ ናቸው።»

ከነዚህ ስድስት በላይ፣ በሌላ መዝገብ ዘንድ ሁለት ሌሎች፣ ሙት-አሽኩር (የእሽመ-ዳጋን ልጅ)፣ እና ሪሙ-... ከእሽመ-ዳጋን በኋላ ይዘርዝራል እንጂ ሌሎቹን አይጠቅስም። ከዚህ በላይ በዚህ ወቅት የባቢሎን (የሃሙራቢ) አገረ ገዥ ፑዙር-ሲን ንጉሡን አሲኑም (የሻምሺ-አዳድ ልጅ-ልጅ) አሞራዊ ስለ ነበር ከዙፋኑ እንዳባረረው በማለት አስቀረጸ። ስለዚህ በተጠቅላላ በነዚህ ፮ ዓመታት ምናልባት ፲ ሰዎች ለአሦር ዙፋን ይወዳደሩ ነበር።

የአሹር-ዱጉል ተከታይ በዝርዝሩ ላይ የተጠቀሰው አዳሲ ልጅ ቤሉ-ባኒ ይባላል። ስለዚህ ያ አዳሲ እንደ አዲሱ አሦራዊ ሥርወ መንግሥት መስራች ይቆጠራል።

የዓመት ስሞች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የያንዳንዱ አሦራዊ ዓመት ስም ለዚያ ዓመት የተሾመው የሊሙ ስም ነበረ። ከዚህ በታች የዓመቱ ሊሙ እና የሊሙ አባት ስም እንደ ኡልትራ አጭር አቆጣጠር ይዘርዝራሉ።[1]

1678 ዓክልበ. - አሁ-ዋቃር
1677 ዓክልበ. - ኪዙሩም
1676 ዓክልበ. - ዳዲያ
1675 ዓክልበ. - ያማሃያ
1674 ዓክልበ. - አዳድ-ባኒ
1673 ዓክልበ. - ኤናም-አሹር፣ አሹር-ታክላኩ ልጅ
1672 ዓክልበ. - አታያ፣ ሻማያ ልጅ
ቀዳሚው
1 እሽመ-ዳጋን
የአሦር ንጉሥ
1678-1672 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ቤሉ-ባኒ

ዋቢ መጽሐፍት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ የመስጴጦምያ ነገሥታት (ፈረንሳይኛ)