አቡነ ዮሴፍ ተራራ

ከውክፔዲያ
አቡነ ዮሴፍ
ጭላዳ ዝንጀሮ በአቡነ ዮሴፍ ተራራ
ከፍታ 4260ሜትር
አቡነ ዮሴፍ is located in ኢትዮጵያ
{{{alt}}}
አቡነ ዮሴፍ

12°9′ ሰሜን ኬክሮስ እና 39°10′ ምሥራቅ ኬንትሮስ


አቡነ ዮሴፍ ተራራላሊበላ በስተስሜን ምስራቅ የሚገኝ፣ ከኢትዮጵያ በከፍታው 16ኛ የሆነ ተራራ ነው። ከባህር ወለል በላይ 4260ሜትር የሚደርሰው ይህ ከፍተኛ ቦታ ከአካባቢው ጠለል ደግሞ በ1909 ሜትር ወደላይ ይጎናል። አቡነ ዮሴፍ ተራራ መቼና መድኃኔ አለምን፣ይምርሃነ ክርስቶስን፣ ጀመዱ ማርያምን፣ ገነተ ማርያምን፣ አሸተን ማርያምንና ሌላ አንድ የአለት ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናንን በማቀፍ በታሪክ ይታወቃል። የእንግሊዙ አርኪዮሎጂ ተማሪ ክራውፎርድ የጨረቃ ተራራ ተብሎ በጥንቶቹ ግሪኮችና አረቦች የሚታወቀው ጀበል ኤል-ካማር ይህ ተራራ እንደነበር ያስረዳል[1]። የጨረቃ ተራራ (ጀበል ኤል ካማር) በኋላ ኢኩየተር በመባል ለምድር ወገብ ስሙን የለገሰ ሐረግ ነው።

የተፈጥሮ ቅርስ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በአቡነ ዮሴፍ ተራራ ላይ በተደረገ ጥናት የ43 አይነት አጥቢ እንስሳት መኖሪያ መሆኑ ሲረጋገጥ፣ 221 አይነት ወፎችም ቤታቸው አድርገው ይኖሩበታል። ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙት ጭላዳ ዝንጀሮ እና ቀይ ተኩላ በዚሁ ቦታ ይገኛሉ ። አቡነ ዮሴፍ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የአዕዋፍ መኖሪያዎች በወፍት ሃብቱ ሁለተኛ ነው[2]


ካርታ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ http://en.wikipedia.org/wiki/Mountains_of_the_Moon_(Africa)
  2. ^ Saavedra, D.; Such-Sanz, À., Díaz, G.; Mariné; R.; Regalado; I. López, M. i L. Dantatrt. (2009) The Mamals of Abune Yosef. In:The Abune Yosef Masif. Birds and Mammals of a hidden jewel of Ethiopia. Eds: Saavedra, D. Pg: 24-70. Centre de Recursos de Biodiversitat Animal. Universitat de Barcelona. Barcelona ኢንተርኔት