አንድምታ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አንድምታ ((እንግሊዝኛ)exegesis) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ውስጥ የመጽሃፍ ቅዱስን ትርጉም ለማወቅ የሚጠቅም የትርጓሜ ሂደት ነው። አንድምታ የሚለው ቃል «አንድም» ከሚለው የአማርኛ ቃል የመጣ ሲሆን የአረፍተ ነገሮችን ድብቅ ትርጉም አውጥቶ ለማሳየት የሚረዳ መሳሪያ ነው። በአንድምታ መጻህፍቶች ውስጥ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት ከሁሉ በላይ ትርጓሜ ያገኘው የዮሐንስ ራዕይ 6፡2 ሲሆን በዚህ ምንባብ የሚገኘው ነጭ ፈረስ 19 አንድምታወች ይዞ ይገኛል[1]

የአንድምታ መጻህፍት የመጽሃፍ ቅዱሳትን እንግዳ ቦታወችና አስተሳሰቦች ከ18ኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያ ቦታወችና አስተሳሰቦች አንጻር በማገናዘብ ያስረዳሉ። ለአንድምታ መነሳትና መስፋፋት ከፍተኛ ሚና የነበረው የፖርቱጋል ካቶሊኮች በአጼ ፋሲለደስ መባረር ነበር። ከዚህ በኋላ በተካሄደው ስራ መምህር ኢሶዶሮስ እና ከሱ በኋላ የተነሳው አቃቤ ሰዓት ሃብቴ በሰፊው ለዚህ ስራ በማበርከት ይጠቀሳሉ። ስለዚህ ሰፊ ጥረታቸው የአንድምታ ትምህርት ከቅኔና ከንባብ ቤት ትምህርት ማለፍ ቀጥሎ የሚሰጥ ልዩ ትምህርት ሆነ።

ማጣቀሻ [ለማስተካከል]

  1. ^ Abraha, Tedros & Kirsten Stoffregen, Encyclopaedia Aethiopica, (edited by Siegbert Uhlig), Harrasowiz Verlag, 2003