እየሩሳሌም
ከውክፔዲያ
ኢየሩሳሌም (ዕብራይስጥ፡- ירושלים ፤ አረበኛ፦ القـُدْس) የእስራኤል ዋና ከተማ ናት። በእስራእል ትልቁ ከተማ ስትሆን የምትገኝው በስተምሰራቅ በኩል ነው። በ3 ሃይማኖቶች (ለአይሁድና፤ ለክርስትና እና ለእስልምና) በጣም የተቀደሰች ናት። የድሮ ታሪኮች ስለሞሏት፣ ብዙ ሰዎች ቱሪስት ሆነው መጥትው ያዩዋታል።
እስራኤል በ1949 እ.ኤ.አ. ዋና ከተማነቱን ከቴል አቪቭ ወደ ምዕራብ ኢየሩሳሌም አዛወረች። በ1967 እ.ኤ.አ. በተዋጀ ጦርነት ምሥራቅ ኢየሩሳሌምን ደግሞ ያዘች። በ1980 እ.ኤ.አ. እስራኤል ሙሉ ከተማውን ዋና ከተማዋ ሆኖ ሾመችው። ነገር ግን አብዛኛው አገራት ይህን አድራጎት ሳይቀበሉ ኤምባሲዎቻቸው እስካሁን በቴል አቪቭ ናቸው የሚገኙ። ፍልስጤም ደግሞ ዋና ከተማውን አድርጎታልና ዛሬም በጣም ተቃራኒ ጉዳይ ሆኗል።
የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 695,500 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 31°47′ ሰሜን ኬክሮስ እና 35°13′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።
| ጅምር! (ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። እርስዎ ሊያስፋፉት ይችላሉ!) |
