ኮንታ

ከውክፔዲያ

ቋንቋ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የኮንታ ብሔረሰብ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ኮንቲኛ ሲሆን፣ ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ ከንግግር ቋንቋነት ባሻገር የትምህርትና የሥራ ቋንቋ በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አብዛኛው የብሔረሰቡ አባላት ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ ዳውሮኛጋሞኛወላይትኛአማርኛ ይናገራሉ።

ሕዝብ ቁጥር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የኮንታ ብሔረሰብ በዋናነነት በኮንታ ልዩ ወረዳ በሚገኙ በገጠር እና የከተማ ቀበሌዎች ውስጥ የሚኖር ሲሆን፣የተወሰኑ የብሔረሰቡ አባላት በተለያየ የሥራ መስክ ተሰማርተው በአጎራባች አካባቢዎች እንደሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የኮንታ ብሔረሰብ የሚገኝበት አካባቢ ሜዳማ፣ ተራራማና ሸለቆ የሆነ መልክአ ምድራዊ ገጽታ ሲኖረው የብሔረሰቡ የኢኮኖሚ መሠረት የሆነው እርሻና ከብት እርባታ ሲሆን፣ የተወሰነው የኀብረተሰብ ክፍል የተለያዩ የዕደ ጥበብ ምርቶች በማካሄድና በማምረት የዕለት ተዕለት ሕይወቱን ይመራል፡፡እንደ 1999 ህዝብና ቤት ቆጠራ መረጃ የኮንታ ህዝብ ብዛት 117,000 በላይ መሆኑን የምጦቅም ብሆንም በተጨባጭ የወረዳው ህዝብ!! ብዛት ከ250,000-300,000 እንደ ማይተናነስ አሁን ከለው የህዝብ አሰፋፈር ሳምፕል ቆጠራ መረዳት ይቻላል ። በወቅቱ ካለው የመሠረቴ ልማት እጥረትና ከመሬት ወጣ ገብነት ጋር ተያይዞ የ1999 መረጃ የተዛባና የአከባቢው የህዝብ ቁጥር መረጃ የማይገልፅ ነው ። በመሆኑም በወረዳው በአሁኑ ሰዓት ያለው ህዝብ ቁጥር ከለላ አከባቢ መተው ከሰፈር ሰፋሪዎች ጋር ከ300,000 በላይ ይገመታል ።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የኮንታ ብሔረሰብ ባህላዊ አስተዳደር መዋቅር ተዋረዳዊ ኃላፊነትና ተግባር ባላቸው የተለያዩ ክፍሎች የተደራጀ ነው፡፡ በእዚህ መዋቅር የሁሉም የበላይ ካዎ ወይም ንጉስ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ከማላ ጎሳ ይመረጣል፡፡ በኮንታ ብሔረሰብ ስድስት ባህላዊ የጋብቻ ዓይነቶች ያሉ ሲሆን፣ እነዚህም በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ቦሣ) የለፋ ጋብቻ (ላታ) በተጋቢዎች ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ማቆ) የቃል ጋብቻ (ያኤኤኩዎ) እና ሚሽቶ (የምትክ ጋብቻ) በመባል ይታወቃሉ፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ ዓይነቶች በብዛት ሲከናወን የሚስተዋለው በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸመው የቦሣ ጋብቻ ነው፡፡

ከብሔረሰቡ ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ፂፄ፣ ጫቻ፣ ዛይ፣ዲንኬ እና ኡልዱዶ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህ የትንፋሽና የምት የሙዚቃ መሣሪያዎች ለለቅሶና ለደስታ ጊዜ ያገለግላሉ፡፡ በተለይ ኡላዱዶ የተሰኘው የትንፋሽ መሣሪያ ከድኩላ ቀንድ ተበስቶ የሚሠራ ሲሆን ከብቶቻቸው ሆራ (ጨውነት ያለው ውሃ) ሊያጠጡ የሚወስዱ እረኞች ይነፉታል፡፡

የኮንታ ባህላዊ የቤት አሠራር ከፍልጥ እንጨት፣ ከቀርከሀ ከሰንበሌጥና ከሣር የሚዘጋጅ ሲሆን በደጋውና በቆላው አካባቢ ልዩነት አለው፡፡

ሱልሶ፣ ሲሊሶ፣ ኡስታ፣ ጨዲያ፣ ኩበዋ፣ ቦሩዋ (ዱቢያ) እና ባጨራ የኮንታ ብሔረሰብ ዋነኛ ባህላዊ ምግቦች ናቸው፡፡ ሲልሶ ለአብነት ከምን እንደሚሠራ እንይ፡፡ ሲልሶ ከጥሬ ሥጋ፣ ከቅቤ፣ ከደም፣ ከሀሞት እና ከተለያዩ የማጣፈጫ ቅመሞች ከተዘጋጀ በኋላ ከተለበለበና በክብ በተቆረጠ የእንሰት ቅጠል ላይ ለቤተሰቡ አባላት ይቀርብና በቡላ ወይም በቆጮ ይበላል፡፡

በብሔረሰቡ ወንዶች ከአቡጀዲ በእጅ የተሰፋ እጀ ጠባብ ሸሚዝና ሱሪ እንዲሁም ሀሲያ የተባለ በእጅ የተፈተለ ልብስ ሲለብሱ ሴቶች በኋላ በኩል ባለወጥ ጥለት የሆነውን ማዳ የተባለ የእጅ ፈትል ይለብሳሉ፡፡

ታዋቂ ሰዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

wende konta ወንዴ ኮንታ

ኮንታ የኢትዮጵያ ብሔር ነው።