ዓፄ ነዓኩቶ ለአብ

ከውክፔዲያ

ንጉስ ነአኩቶ ለአብቅዱስ ላሊበላ የወንድም ልጅ ነው አባቱ ሐርበይ እናቱ መርኬዛ ይባሉ ነበር። ይህ ጻድቅ፤ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ ክህነትን ከንግስና ይዘው ኢትዮጰያን ከመሩ አራቱ የዛጌ ነገስታት አንዱ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለነዚህ አራት ነገስታት ጽላት ቀርጻ እና ቤተክርስቲያን አሳንጻ እንዲሁም የቅድስና ስም ሰጥታቸው ታከብራቸዋለች። እኒሁም ይምርሃነ ክርስቶስላሊበላነዓኩቶ ለአብ እና ገብረ ማርያም ናቸው። እንደ ንጉሱ ገድል ታሪክ፣

ነአኩቶ ለአብ በነገሰበት 40 ዓመት ሙሉ አርብ አርብ ቀን የክርስቶስን ህማም እያሰበ በዘውዱ ፋንታ የእሾህ አክሊል ደፍቶ፤5 ጦር ዙሪያውን ተክሎ እየደማ እያለቀሰ ሲጸልይ ሲሰግድ ይውል ነበር። ከእለታት በአንዱ ቀን ጌታችን ተገለጸለት እንዲህም አለው ወዳጄ ነአኩቶ ለአብ እኔ ለዓለም ደሜን ያፈሰስኩት አንድ ቀን ነው፤ አንተ ግን 40 ዓመት ሙሉ ደምህንንና እንባህን ስታፈስ ኖርክ ይበቃሃል አሁን ወደ እኔ ልወስድህ ነው ይለዋል፤ነአኩቶ ለአብም ጌታችንን “ጌታዬ ሆይ እዚህ ቦታ እኔን ብለው የሚመጡ ወገኖቼን ማርልኝ ይለዋል” ጌታም እውነት እልሃለው ቦታህን ባይረግጥ ዝክርህን ባያዘክር እንኳን ዝናህን ሰምቶ ያሰበህን ኃጢያቱ ምን ቢበዛ እምርልሃለው፤ ዳግመኛም እልሃለው 40 ዓመት ሙሉ እንባህን ያፈሰስክባት ይህች ድንጋይ እስከ እለተ ምጽአት እያነባች ትኖራለች ከዚህ ለሚጠጡ ለሚጠመቁ ድህነት ይሁናቸው ብሎታል።

ዛሬም ድረስ የነአኩቶ ለአብ ቤተክርስቲያኑ ባለበት ከጣራው ስር ጻበሉ እየቆየ ጠብ ጠብ ይላል፤ክረምት ከበጋ እይለይም እንዲያውም በበጋ መጠኑ ይጨምራል[ዋቢ መጻሕፍት ያስፈልገዋል]። እንደገድሉ ታሪክ፣ ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ አሸተን ማርያምን አንጾ ከጨረሰ በኃላ ማዕጠንት ይዞ ቤተክርስቲያኑን ሲያጥን ብዙ ቅዱሳን እጣኑን አሽትተው ቤተክርስቲያን ውስጥ ጥቅጥቅ ብለው ቆሙ፤ እናንተ ደግሞ እንዴት መጣችሁ አላቸው እነርሱም እጣኑን አሽትተን መጣን አሉት በዚህም የተነሳ “አሸተን ማርያም ” ተብላለች።

ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ በ70 ዓመቱ ህዳር 3 ቀን አረፈ። እንደርሱ ገድል፣ ነዓኩቶ ለአብ እንደ ሄኖክ በዚህ ቀን አረገ።

ዋቢ መጻሕፍት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • የይምርሃነ ክርስቶስና የነአኩቶ ለአብ ገድል