የአሜሪካ ብሔራዊ ጦርነት

ከውክፔዲያ
የአሜሪካ ብሔራዊ ጦርነት

የአሜሪካ ብሔራዊ ጦርነት1853 እስከ 1857 ዓም ድረስ በአሜሪካ ክፍላገራት መካከል የሆነ የእርስ በርስ ጦርነት ነው። ባርነት እስከዚያ ድረስ ሕጋዊ የነበረባቸው ደቡባዊ ክፍላገራት ተገንጥለው የራሳቸውን መንግሥት የአሜሪካ ኮንፌደራት ክፍላገራት አወጁ። በፕሬዝዳንት አብርሀም ሊንከን መሪነት ግን፣ ወደ ስሜን የቀሩት ተባባሪ ክፍላገራት አሸንፈው ኮንፌደራቶቹን ድል አደረጓቸውና ደቡቡን ወደ ኅብረቱ በግድ አስመለሱ። በአራት አመት ጦርነት ውስጥ ምናልባት 1 ሚልዮን ሰዎች ጠፉ። በአገሩ ውስጥ የነበሩት አራት ሚልዮን ባርዮች ያንጊዜ ነጻነታቸውን አገኙ፣ ባርነትም በሕገ መንግሥት ለውጥ ተከለከለ።