የኢትዮጵያ አየር መንገድ
ከWikipedia
|
|
|||
| ድርጅት | የኢትዮጵያ አየር መንገድ | ||
| ሊቀ መንበር | አቶ ስዩም መስፍን | ||
| ዋና አስፈጻሚ ባለ ሥልጣን | አቶ ግርማ ዋቄ | ||
| ማእከላዊ ጣቢያ | ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ | ||
| የሠራትኞች ብዛት | 4 850 (ሰኔ 2008 እ.ኤ.አ) | ||
| የመንገደኞች ብዛት (በዓመት) | 2 095 564 (እስከ ሰኔ 2007 እ.ኤ.አ) | ||
| የመንገደኛ አውሮፕላኖች | 10 ቦይንግ 767-300; 8 ቦይንግ 757-200፤ 5 ቦይንግ 737-700NG፤ 5 ፎከር 50 | ||
| የጭነት አውሮፕላኖች | 1 ቦይንግ 757-260F፤ 1 ቦይንግ 757-200PCF፤ 1 ቦይንግ 747-400F፤ 1 AN-12፤ 1 MD-11F | ||
| ድህረ ገጽ | http://www.ethiopianairlines.com | ||
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና መሥሪያ ቤቱ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ የሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አየር መንገድ ድርጅት ነው። አየር መንገዱ ከቀድሞው ትራንስ ወርልድ ኤየርዌይስ/ Transworld Airways (TWA) ጋር በጋራ የተመሠረተ ሲሆን አስተዳደሩ በአሜሪካኖች እጅ ነበር፤ ድርጅቱ እ.ኤ.አ 30th December 1945 ተመሥርቶ ለመጀሜሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ በረራውን እ.ኤ.አ April 8, 1946 ከአዲስ አበባ ካይሮ አከናወነ።
አየር መንገዱ ሲመሠረት ከአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል የተገዙና በሁለተኛው ዓለም ጦርነት ያገለገሉ አምስት ዲ.ሲ. 3 (DC 3-C47) አውሮፕላኖች ነበሩት። በዓለም ዙሪያ በአፍሪካ፤ በእስያ፤ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ክፍለ አህጉራት ወደ 50 የመንገደኛና የጭነት አገልግሎት ሲሰጥ፤ በሀገር ውስጥ ደግሞ በአሁኑ ጊዜ 16 መድረሻዎችን ያገለግላል። ዋና የጣቢያው ማዕከል በአዲስ አበባ የሚገኘው [[ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ]] ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የራሱ የአውሮፕላን አብራሪዎች ማሰልጠኛ ትምሕርት ቤት ሲኖረው የግል አብራሪ እና የንግድ አውሮፕላን አብራሪ ፈቃድ በመስጠት የሀገር ልጆችንም ሆነ የውጭ ዜጎችን በማሰልጠን እስከ አርባ ዓመት ልምምድ አለው። እንዲሁም ለብዙ የአፍሪካ ሀገር ብሔራዊ አየር መንገዶችና የግል አውሮፕላኖች የጥገና አገልግሎት ይሰጣል።
አየር መንገዱ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግሥት የተያዘ የኢትዮጵያውያን ሀብት ሲሆን፤ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ለሽያጭ እና ለግዢ እንዲሁም ለብድር አመቺ እንዲሆን ተብሎ በአየር መንገዱ ሙሉ ቁጥጥር ሥር በ ኬይማን ደሴቶች (Cayman Islands) የተመሠረተ ድርጅት ባለቤት ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ለመንገደኞች አገልግሎት አዲሱንና ዘመናዊውን የቦይንግ (Boeing) 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን በማዘዝና ጥቅም ላይ በማዋል ከአፍሪካ የመጀመሪያው አየር መንገድ ሊሆን ነው። የታዘዙትን 10 ቦይንግ 787 ድሪምላይነር (Boeing 787 Dreamliner) አውሮፕላኖች እ.አ.አ. በ2009 መጨረሻ ላይ እንደሚረከብና ጥቅም ላይ እንደሚያውል ይጠበቃል። ከዚህ በተጨማሪ አየር መንገዱ 8 ቕ400 አውሮፕላኖች ከቦምባርዲየር (Bombardier ለሀገር ውስጥ መንገደኞት አገልግሎት አዟል።
፲፱፻፹፱ ዓ.ም. ዓለማየሁ በቀለ በላይነህ፣ ማትያስ ሰሎሞን በላይ እና ሱልጣን አሊ ሁሴን የተባሉ ሦስት ኢትዮጵያውያን፣ ከአዲስ አበባ ተነስቶ በናይሮቢ በኩል ወደቦምቤይ በረራ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ ዓየር መንገድ በረራ ቁ. ፱፻፷፩ በዓየር ላይ ጠለፉ። በጠለፊዎቹም ትእዛዝ ወደ አውስትራሊያ ሲያመራ ነዳጅ በመጨረሱ ምክንያት በረራው በሕንድ ውቅያኖስ ላይ ወደምትገኘው የቆሞሮስ ደሴት ተጠግቶ ከደሴቷ ግማሽ ኪሎሜትር ውቅያኖሱ ላይ ሊያርፍ ሲሞክር የዓየር ተሽከርካሪው ተሰባብሮ ፈነዳ። ከመንገደኖቹም ውስጥ፣ ጠላፊዎቹን ጨምሮ መቶ ሃያ ሦሥት ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። ከሞቱት መንገደኞች አንዱ፣ ኬንያዊው የፎቶ-ጋዜጠኛ ሞሐመድ አሚን ነበር