የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በሀገሪቱ ውስጥ ከፍተኛው የስፖርት ክንውን ነው። ይህ ሊግ በየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስር የሚተዳደር ሲሆን በየጊዜው የተለያዩ ስፖንሰሮች ደግፈውታል። ሊጉ በየ አመቱ የሚከናወን ሲሆን በ አመት ውስጥ በሁለት ክፍል (ሲዝን) ተከፍሎ ይካሄዳል። ሊጉን ለማሸነፍ አንድ ክለብ ከፍተኛ ነጥብ ይዞ አመቱን መጨረስ ይጠበቅበታል። ክለቦች እርስ በእርሳቸው በአመት ሁለት ግዜ ይገናኛሉ። እያንዳንዱ ክለብ አንድ ጨዋታ በ ራሱ ሜዳ ሌላውን በባላጋራ ክለብ ሜዳ ያከናውናል።
ማውጫ |
ታሪክ [ለማስተካከል]
የኢትዮጲያ ፕሪሚየር ሊግ የተመሰረተው በ 1994 ዓ.ም. ነው። የሊጉ አርማ ከዚህ በላይ የሚገኘው ነው። ይህ ሊግ በ እ.አ.አ.2009/10 የውድድር ዘመን በ 18 ክለቦች እየተከናወነ ነው። የሊጉ ችግሮች ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል አብዘሃኛው ጨዋታዎች በአዲስ አበባ ስታዲየም መካሄዳቸው ነው። ይህን ችግር ለመቅረፍ ይመስላል የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ የራሱን ስታዲየም በ ዶ/ር ሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ እና በደጋፊው መዋጮ የራሱን ስታዲየም በማስገንባት ላይ ነው። ይህ ሊግ በ እ.አ.አ. 2007 ችግር አጋጥሞት ነበር። ለዚህም ቺግር 12 የ ሊጉ ክለቦች ( ሰባቱን የአዲስ አበባ ክለቦች ጨምሮ ማለት ነው። ) ራሳቸውን አግልለው ነበር። በዚህ ግዜ ፌዴሬሽኑ ዋንጫውን ለ ሃዋሳ ከነማ ክለብ ሰጥቷል። ኢትዮጵያ በ አለም አቀፉ የ እግር ኳስ ማህበር ፊፋ እስከመታገድ የደረሰችበት ግዜ ነበር። ይህ እገዳ ከብዙ አለም አቀፍ ውድድሮች እንድትታገድ ያደረጋት ሲሆን እገዳው በቅርቡ ተነስቶላታል። ሊጉ በአሁኑ ሰአት በቀድሞው አመራሮች መመራቱ ቀርቶ በ አዲስ አመራሮች መመራት ጀምሯል።
ከፍተኛ ግብ አግቢዎች [ለማስተካከል]
2007/8 ሳልሃዲን ሰይድ በተጠቀሰው አመት ከፍተኛ ግብ አግቢ ሁኖ ጨረሰ። ያገባቸው ጎሎች ብዛት 21 ነው። ተጫዋቹ የቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ ተጫዋች ነው።
ብዙ ግዜ ማሸነፍ [ለማስተካከል]
ሊጉን በተደጋጋሚ በማሸነፍ ደረጃውን የያዙት ክለቦች የሚከተሉት ናቸው፡
- 20 (ሃያ) ግዜ..............................ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ
- 6 (ስድስት) ግዜ..........................መቻል የእግር ኳስ ክለብ
- 5 (አምስት) ግዜ..........................ጦር የእግር ኳስ ክለብ
አሸንፈዋል።
ጦር የእግር ኳስ ክለብ እ.አ.አ. ከ 1951 እስከ 1954 በተከታታይ 4 (አራት) ግዜ በማሸነፍ ታሪክ ያለው ክለብ ነው። ይህ ክለብ በአሁኑ ግዜ የለም። አሁን ካሉት ክለቦች ደግሞ ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ እ.አ.አ. ከ 1994 እስከ 1996 በተከታታይ ለ3 (ሶስት) ግዜ ያህል በማሸነፍ ብቸኛው ክለብ ነው። በደጋፊ ብዛትም ቢሆን ብልጫውን እንደሚይዝ ብዙዎች ይናገራሉ።
ድረ ገጽ ያላቸው [ለማስተካከል]
በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ክለቦች የራሳቸው የድረ ገጽ አድራሻ ያላቸው ክለቦች 2 (ሁለት) ብቻ ናቸው። እነርሱም፡ ኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ክለብ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ ናቸው። በይዘቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ ድህረ ገጽ (http://www.saintgeorgefc.com/) ስለ ክለቡ እና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የተሻለ መረጃ እንደሚሰጥ አንድ የኢትዮጵያ ጋዜጣ ዘግቧል። በአንጻሩ የኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ክለብ ድህረ ገጽ (http://www.ethiopiancoffeesportclub.com/) በየጊዜው ያሉ መረጃዎችን በማቅረቡ ረገድ ያልተሳካለት መሆኑንም ነው ጋዜጣው የዘገበው።
የሊጉ ተሳታፊ ክለቦች [ለማስተካከል]
በሊጉ ውስጥ በ፳፻፫ ዓ.ም. የሚሳተፉ ክለቦች 18 (አስራ ስምንት) ናቸው። እነዚህም፦
- ሐረር ቢራ የእግር ኳስ ክለብ
- መብራት ኃይል የእግር ኳስ ክለብ
- መተሓራ ስኳር የእግር ኳስ ክለብ
- መከላከያ የእግር ኳስ ክለብ
- መድን የእግር ኳስ ክለብ
- ሙገር ሲሚንቶ
- ሜታ አቦ የእግር ኳስ ክለብ
- ሰበታ የእግር ኳስ ክለብ
- ሲዳማ ቡና የእግር ኳስ ክለብ
- ቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ቡድን
- ባንኮች የእግር ኳስ ክለብ
- ትራንስ የእግር ኳስ ክለብ
- ኒያላ የእግር ኳስ ክለብ
- አዋሳ ከተማ የእግር ኳስ ክለብ
- አዳማ ከተማ የእግር ኳስ ክለብ
- የኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ክለብ
- ደቡብ ፖሊስ የእግር ኳስ ክለብ
- ድሬዳዋ ከነማ የእግር ኳስ ክለብ
