ዳግማዊ ምኒልክ

ከWikipedia

ዘልለው ለመሐድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ምኒልክ
ምኒልክ

[ለማስተካከል] ጥቅስ

«እናንተ አንድ ልብ ከሆናችሁ በምቀኝነት እርስ በርሳችሁ ተዋግታችሁ ካላለቃችሁ በቀር አገራችንን ኢትዮጵያን ለሌላ ለባእድ አትሰጧትም፤ ክፉም ነገር አገራችንን አያገኛትም። ነፋስ እንዳይገባባችሁ አገራችሁን በያላችሁበት በርትታችሁ ጠብቁ፤ ወንድሜ ወንድሜ እየተባባላችሁ ተደጋገፉ፤ የኢትዮጵያን ጠላት ተጋግዛችሁ ተደንበር መልሱ። የኢትዮጵያ ጠላት ባንዱ ወገን ትቶ ባንድ ወገን ቢሄድና ደንበር ቢገፋ፤ በኔ ወገን ታልመጣ ምን ቸገረኝ ብላችሁ ዝም አትበሉ፤ ያ ጠላት በመጣበት በኩል ኁላችሁም ሄዳችሁ አንድነት ተጋግዛችሁ ጠላታችሁን መልሱ እስከ እየቤታችሁ እስኪመጣ ዝም ብላችሁ አትቆዩ» [1]

ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ፤ ግንቦት 10 ቀን 1901 ዓ.ም.

[ለማስተካከል] ቅደም ተከተል

ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ከአባታችው ከሸዋው ንጉስ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሤና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አዲያሞ ቅዳሜ ነሐሴ 12 ቀን 1836 ዓ.ም. ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ በአንጎለላ መቅደላ ኪዳን ምሕረት ክርስትና ተነሱ።

በጥቅምት ወር 1848 ዓ.ም. ጃንሆይ ምኒልክ ገና የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ሳሉ፤ ዓፄ ቴዎድሮስ የድፍን አማራንና የወሎን ጦር አስከትተው የሸዋውን ንጉሥ ኃይለ መለኮትን ለማስገበር ሸዋ ገቡ። ሁለቱ መሪዎች ጦርነት ለመግጠም ተዘጋችተው ሲጠባበቁ ንጉሥ ኃይለ መለኮት ባደረባቸው ሕመም ኅዳር 30 ቀን አረፉ። በዚህ ጊዜ የሸዋ መኳንንት ሕጻኑን ምኒልክን ከጠላት እጅ እንዳይወድቅባቸው ይዘው ሸሹ፤ ዳሩ ግን ዓፄ ቴዎድሮስ እንደሚከታተሏቸው ስላወቁ ሕጻኑን ይዘው ገቡ። ምኒልክም ዓፄ ቴዎድሮስ ዘንድ መቅደላ ላይ በቁም እሥር ይቀመጡ እንጂ ከቴዎድሮስ ልጅ ከመሸሻ ጋር አብረው አደጉ። ወዲያውም የደጃዝማችነት ማዕረግ ተሹመው በጥር ወር 1856 ዓ.ም የዓፄ ቴዎድሮስን ልጅ ወይዘሮ አልጣሽን አገቡ። በዚህ ሁኔታ እድሜያቸው 22 ዓመት ድረስ ለ 10 ዓመታት ዓፄ ቴዎድሮስ ግቢ ኖሩ።

ዳግማዊ ምኒልክ፣ ንጉሥንጉሠ ነገሥት (1844 እ.ኤ.ኣ. - 1889 እ.ኤ.ኣ. - 1913 እ.ኤ.ኣ.)፣ ኢትዮጵያ

[ለማስተካከል] ዋቢ መፃሕፍት

  1. ዳግማዊ አጤ ምኒልክ፤ አፈወርቅ ገብረኢየሱስ 1901 ዓ.ም ገጽ 114
የኔ መሣርያዎች