ከWikipedia
በ 'አብርሃማዊ ሀይማኖቶች' (ክርስትና ፤ አይሁድ ፤ እስልምና) ገብርኤል (ቅዱስ ገብርኤል) ከሶስቱ ዋና መላዕክት (ሚካኤል፡ ገብርኤል፡ ሩፋኤል) አንዱ ሲሆን በእግዚአብሔር መልእክተኛነቱ ይታወቃል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰው በመጽሐፈ ዳንኤል ነው። የስሙም ትርጉም "ከእግዚአብሔር የሆነ አለቃ" ማለት ነው። በእግዚአብሔር ፊት መቆም ከሚችሉ ስባት መላዕክት ውስጥም አንዱ ተደርጎ ይቆጠራል።
-