ገብርኤል (መልዐክ)
ከውክፔዲያ
ገብርኤል (ቅዱስ ገብርኤል) በአብርሃማዊ ሀይማኖቶች (ክርስትና ፤ አይሁድ ፤ እስልምና) ከሶስቱ ዋና መላዕክት (ሚካኤል፡ ገብርኤል፡ ሩፋኤል) አንዱ ሲሆን በእግዚአብሔር መልእክተኛነቱ ይታወቃል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሰው በመጽሐፈ ዳንኤል ነው። የስሙም ትርጉም «ከእግዚአብሔር የሆነ አለቃ» ማለት ነው። በእግዚአብሔር ፊት መቆም ከሚችሉ ስባት መላዕክት ውስጥም አንዱ ተደርጎ ይቆጠራል። የአምላካችን፣ የጌታችንና የመድሐኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ለቅድስት ድንግል ማርያም አብስሯል።