ጠይት

ከውክፔዲያ

ጠ ጡ ጢ ጣ ጤ ጥ ጦ ጧ



አቡጊዳ ታሪክ

ጠይት (ወይም ጣይት) በአቡጊዳ ተራ ዘጠነኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥና በሶርያ ፊደሎች ዘጠነኛው ፊደል "ጤት" ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል "ጣእ" ተብሎ በ"አብጃድ" ተራ 9ኛ ነው። (በዘመናዊ ተራ ግን 16ኛው ነው።)

አማርኛ ደግሞ "ጨ ጩ ጪ ጫ ጬ ጭ ጮ" ከ"ጠ..." ትንሽ ተቀይሯል።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል (?) ሣባ ግዕዝ
O49


የጠይት መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ቢታስብም እስካሁን አልተገኝም። በከነዓን ጽሕፈት ፊደሉ የመንኮራኩር ስዕል መስለ። ለዚህም ምናልባት ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ "ኒውት" ("መንደር") ነበር። አንዳንድ ሊቃውንት ግን ሌላ ስዕል "ጥሩ" ("ነፈር") እንደ ነበር ይገምታል።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
ዘይ ዘይ ט ዘይ


የከነዓን "ጤት" የዕብራይስጥና የአራማያ "ጤት" የአረብኛም "ጣእ" ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት "ጤታ" (Θ, θ) አባት ሆነ። እነዚህ የ"ጠይት" ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር (ዘጠኝ) ከግሪኩ θ በመወሰዱ እሱም የ"ጠ" ዘመድ ነው።