ጣና ሐይቅ
ጣና ሐይቅ የአባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ምንጭ ሲሆን ከኢትዮጵያ አንደኛ ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር እርግጠኛ መሆን ባይቻልም ብዙ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በደጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ።
የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማሬ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ።
[ለማስተካከል] የዓሳ ምርት
አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው።
[ለማስተካከል] ታሪካዊ የጣና ክፍሎች
| ኢትዮጵያ |
|
ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ |
