ጳውሎስ ኞኞ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አቶ ጳውሎስ ኞኞ

ደራሲ ጳውሎስ ኞኞ ኅዳር 11 ቀን 1926 ዓ.ም ቁልቢ አካባቢ ተወለደው ድሬዳዋ ከተማ አደጉ። በጣሊያን ወረራ ምክንያት ትምህርታቸውን ከ4ኛ ክፍል በላይ ለመቀጠል አልቻሉም ነበር። ብልህ አዕምሮና የፈጠራ ችሎታ የነበራቸው ሰው ስለነበሩ፤ በልጅነታችው የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ጣሊያንን ሲገድሉ ወይንም ሲማርኩ ሥዕል በመሣል ያሳዩ ነበር። ጳውሎስ ካላቸው የጽሑፍ ጥማት የተነሳ የ«ድምጽ ጋዜጣ» አዘጋጅ በመሆን የብዕር ድምጻቸውን ያሰሙ ነበር። ጋዜጦች ላይ ከጽሑፍ አቅራቢነት እስከ አዘጋጅነት ለበርካታ ዓመታት ሠርተዋል። በተለይ «አንድ ጥያቄ አለኝ» በሚለው የአዲስ ዘመን ጋዜጣ አምዳቸው ላይ ብዙ ታዋቂነትን አግኝተዋል። አቶ ጳውሎስ ኞኞ ከ1955 ዓ.ም ጀምሮ ለኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ዕድገት የነበራቸውን ተሰጥኦ በአግባቡ በሥራ ላይ ያዋሉ እውቅ ጋዜጠኛና ደራሲ ነበሩ።[1] እኚህ ታዋቂ ሰው በተወለዱ በ58 ዓመታቸው ሞቱ።

አቶ ጳውሎስ የጌታችው ሚስቶች በሚል ርዕስ ያሳተሟትን መጽሐፍ፤ «ከታተመችበት ወር አንሥቶ ላንድ ዓመት የመጽሐፌ መብት የግሌ ነው፡ ከአንድ ዓመት በኋል መብቱ የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ይሁን፡ ከወሰንኩት ጊዜ በኋላ አሳትሞ ለመሸጥ የፈለገ ሁሉ ከድርሰቴ ሳይቀንስም ሆነ ሳይጨምር ሊያራባው ይችላል። ስሜን ሳይሰርዝ 'አሳታሚውን እገሌ' ብሎ ማንም ኢትዮጵያዊ ከፈለገ እንዲያራባት የደራሲነት መብቴን ልቅቄአለሁ፡ አሳታሚው የግሉን የመግቢያ ሐተታ በስሙ ቢጽፍ እኔም ሆንኩ ወራሼ አንቃወምም።» ብለዋል

ማውጫ

[ለማስተካከል] የጳውሎስ ኞኞ ድርሰቶች

[ለማስተካከል] አጫጭር ልብ ወለዶች

  • ከሴቶቹ አምባ
  • የአራዳው ታደሰ
  • የጌታቸው ሚስቶች
  • ድብልቅልቅ
  • የኔዎቹ ገረዶች

[ለማስተካከል] ታሪካዊ መጻሕፍት

[ለማስተካከል] ጥቅስ

ስለጸሐፊነት ባህሪያቸው ሲጽፉ፦ «'ይምሰል አይምሰል የጠይብ እጅ ከከሰል' እንደሚባለው እጄ እንደልማድ ሆኖበት መሞጫጨርን ይወዳል፡ ያን ሟጫራዬን ደግሜ ካነበብኩ ቀድጄ መጣል ነው፤ ይሰለቸኛል፡ እጠለዋለሁ፡ ስለዚህ አንድ ጊዜ በማርቀቅ የጻፍኳትን እንድትታተም እፈርድባታለሁ። ምናልባት አባጣ ጎባጣ ሆኖ አላስኬድ የሚል ገደላገደል ቢያጋጥማችሁ በደምዳሜ እመር እያላችሁ አላፉት።» [2]

[ለማስተካከል] ማስታወሻ

  1. ^ ብሔራዊ ቢብሎግራፊ (የደራሲያን አጭር የሕይወት ታሪክ) ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. [1]
  2. ^ የጳውሎስ ኞኞ ስብስብ ሥራዎች፦ ድብልቅልቅ ፳፻ ዓ.ም.
የኔ መሣርያዎች

Variants
Actions
የማውጫ ቁልፎች
ጠቃሚ መሣሪያዎች