መጋቢት ፳፬
(ከመጋቢት 24 የተዛወረ)
መጋቢት ፳፬፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፬ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፹፱ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፷፪ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፷፩ ቀናት ይቀራሉ።
ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፳፻፲ ዓ.ም. - ዶ/ር ዓቢይ ኣሕመድ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ።
- ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽና ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴ፣ ንጉሥ ተፈሪ መኮንን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተብለው በንጉሠ ነገሥት ዙፋን ተቀመጡ፡፡
ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፲፱፻፵ ዓ.ም - የእንስሳት ሕክምና ባለሙያውና የግዕዝ ፊደላትን በኮምፕዩተር ለመጀመሪያ ጊዜ መጠቀም እንዲቻል ያደረጉት ምሁር ዶ/ር ኣበራ ሞላ በዚህ ዕለት ተወለዱ።
ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ በነገሡ በአሥራ ሦሥት ዓመት ተኩል በ፶፬ ዓመት ዕድሜያቸው ዐረፉ። የሞታቸው ዜና እንደተሰማም በከተማው የሐዘን ጥላ አጠላበት። አባታቸው ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ በተቀበሩበት በታዕካ ነገሥት በዓታ ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ።
- ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - የካቶሊኩ ሊቀ ጳጳስ ዳግማዊ አቡነ ዮሐንስ-ጳውሎስ በ፹፬ ዓመት ዕድሜያቸው አለፉ።
ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፣ ዕለታዊ የታሪክ ድርጊት - የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያው ፓትሪያርክ (፲፱፻፶፩ ዓ/ም)
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |