ታኅሣሥ ፳፱
(ከታኅሣሥ 29 የተዛወረ)
ታኅሣሥ ፳፱ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፱ ኛው ዕለት ሲሆን፤ ከዚህ ቀን በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፪፻፵፯ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ ዘመነ ማቴዎስ እና በዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፵፮ ቀናት ይቀራሉ። እንዲሁም በኢትዮጵያ ባሕረ ሐሳብ ታኅሣሥ ፳፱ ቀን የበጋ ወቅት አራተኛው ዕለት ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከዘመነ ዮሐንስ በስተቀር፣ በዚህ ዕለት የጌታችን፣ መድኅኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ታከብራለች። በዘመነ ዮሐንስ ልደት የሚውለው በታኅሣሥ ፳፰ ቀን ነው።
ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - አረባዊ ነዳጅ አምራች አገሮች በወቅቱ የነዳጅ ምርታቸውን የፖለቲካ መሣሪያ በማድረጋቸው በአፍሪቃውያን አገሮች ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ ለማጥናት የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባዔ አዲስ አበባላይ ተሰበሰበ።
- ፲፱፻፹፰ ዓ/ም - አንቶኖቭ-፴፪ የተሰኘው የኤየር አፍሪክ የጭነት አየር-ዠበብ ከኪንሻሳው እንዶሎ ማረፊያ ጭነት አብዝቶ ለመነሳት ሲያኮበኩብ አካባቢው የሚገኘው ገበያ ላይ ተከስክሶ ፫፻ ሰዎችን ሲገድል ፪፻፶፫ ሰዎች ደግሞ ከባድ አደጋ ደርሶባቸዋል።
ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |