Jump to content

ህገ ጉልበት ጥበቃ

ከውክፔዲያ

ህግ ጉልበት ጥበቃ የ ልዩ ስርኣት ጠቅላላ ጉልበት እንደማይለወጥ ይገልጻል ፤ ማለትም በ ጊዜ ለውጥ ሂደት ውስጥ ጠቅላላ ጉልበት ይጠበቃል። በ ህጉ መሰረት ለ ዝግ ስርኣት በ ውስጡ ያለው ጠቅላላ ጉልበት ሊለውጥ የሚችለው ጉልበት ወደ ስረአቱ ሲገባ ወይም ሲወጣ ነው። ጉልበት ሊፈጠርም ሆነ ሊጠፋም አይችልም ነገር ግን ከ አንድ አይነት ቅርጽ ወደ ሌላ አይነት ቅርጽ ሊለወጥ ይችላል። ለ ምሳሌ ዳይናማይት ሲፈነዳ ከሚካዊ ጉልበቱ ወደ ቅስቃሴ ጉልበት ይለወጣል። በ ፍንዳታው ጊዘ የ ተለቀቁትን ሁሉንም የ ጉልበት አይነት ቅርጾችን ብንደምራችው ማለትም የ ፍርክሽካሾችን ክሂሎታዊ ጉልበት እና ቅስቃሴ ጉልበት እንዲሁም የ ሙቀት እና ድምጽ ጉልበት በ ጠቅላላው ይ ዳይናማይቱ ከሚካዊ ጉልበት የ ቀነሰበትን ዋጋ እናገኛለን።

እንደ ነባሩ ፊዚክስ ህገ ጉልበት ጥበቃ እና ህገ ጥበቃ የተለያዩ ህጎች ነበሩ ፤ ነገር ግን በ ልዩ ንጽጽራዊ ጽንሰ ሃሳብ መሰረት በ መጠነ ቁስ እና በ ጉልበት መካክል ይህን እኩለታ “ E=mc2” በ መጠቀም የ መጠነ ቁስ ጉልበት እኩልነትን በ አጠቃላይ ይጠብቃል። መጠነ ቁስ ወደ ጉልበት ጉልበትም ወደ መጠነ ቁስ መለወጥ ይችላል ፤ በ አተማዊ ኒኩለስ እንደመንመለከተው መጠነ ቁሱ ከምጠበቀ በታች ነው ይህም የሚሆነው ወደ ኒኩላዊ አጣማጅ ጉልበት ስለሚቅየር ነው። አስፈላጊነቱም ከፍ ያለ ደረጃ የሚሆነው በጣም ከባድ የሆኑ ተፈጥራዊ ሁነታዎች ላይ ልክ ሁለንተናዊ አለም በ አብይ ፍንዳታ ሲፈጠር የ መጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች ላይ እና የ ጨለማው ጉድጓድ ሃውኪንግ ጨረራ ሲለቅ ዪጠቀሱበታል። የ ጉልት ግብር መርህን መሰረት በማድረግ እንዱሁም የ ኖኤተርን ጽንሰ ሃሳስብ በ መጠቀም ህገ ጉልበት ጥበቃ እንደ ቀጣይ የ ጊዜ ሽግግር ሚዛናዊነት ውጤት ይታያል። ይህም ማለት “ህጋጋተ ፊዚክስ ከ ጊዜ ጋር አይለዋወጥም።”

ከ ህገ ጉልበት ጥበቃ ውጤቶች አንዱ ለዘላለም እየተንቀሳቀሰ የሚሰራ ማሽን ሊኖር አለምቻሉን ማረጋገጡ ነው። ይህም ማለ ምንም አይነት ስረአት ያለ ጉልበት ሰጪ አካል ለ አካባቢው ገደብ የለሽ ጉልበት ሊሰጥ አይችልም። እንድ ሁነታው አስፈላጊነት በ ጥዕቅላይ ንጽጽራዊ ጽንሰ ሃሳብ እና በ ስነ ኮሞስ ህገ ጉልበት ጥበቃ ሊጣስ ይችላል። በ መካኒክሰ ደቂቅ ግን ለ ኖኤተር ጽንስ ሃሳብ ተገዚ ለሆኑ ሁነቶች ስለሚያገለግል ዘላቂነት ያለ ህገ ጉልበት በቃ ሊኖር አይችልም። (ግን አለም አቀፍ ስምምንት ላይ አልተደረሰም)

ታርካዊ አመጣጥ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ከ ማንቲሱ ታለስ(4943 አ.አ) ጀምሮ ጥንት ፈላስፎች ሁሉም ነገር የተፍጠረበትን ንጥረ ነገር የሚገዛ ህገ ጥበቃ እንዳለ ለማመን ዝንባለ ያሳዩ ነበር ፤ ነገር ኝ አሁን ካለው የ ጥበቃ ህግ ጋር ለማስተሳሰር በቂ ምክኛት ወይም ማስረጃ የለም። ለ ምሳሌ ያህል ታለስ ውሃ ነው ብሎ ያስብ ነበር፣ እምፖደስ(5003-5043 አ.አ) ሁለንተና አለም ከ አራት ንጥረ ነገሮች (ንፋስ ፣ አየር ፣ ውሃ ፣ እሳት) ተሰርቷል ብሎ ያምን ነበር። “ምንም አልተፈጠረም ፣ ምንም ዐይፈጠርም ነገር ግን እነዚህ ንጥረ ነገሮች መልሰው ይዋቀራሉ”። እፒኩረስ(5150 አ.አ) ሁለንተናዊ አለም ከ ደቂቅ ወደ ትንሽ አካላት ሊለወጡ የ ማይችሉ ንጥረ ነገሮች እንደተሰራ ያምን ነበር ይህም አመለካከት ለ አተም ፍልስፍና ፈር ቀድዷል። “የሁሉም ነገር ድምር ሁሌም እንደነበረ ነው እንደዛአውም ይሆናል”።

በ 1598 ዓ.ም ፍለማዊው ተመራማሪ ስይመን ስቲቨን የ ዘላለማዊ እንቅስቃሴ አለመቻል መርህን ተጠቅሞ እምብዛም ስታቲቻዊ ትራጊሎችን ሊፈታ ችሏል።

በ 1632 ዓ.ም ጋሊሎ በ ተለያዩ ሁነቶች ላይ ሳይንሳዊ ትንተናውን አሳተመ ፤ ከነዚህም ውስጥ በጣም ታዋቂው “የ ተነካ ፐንዱሉም” በ ዘመናዊ ቋንቋ ሲገለጽ በ ህግ ጉልበት ጥበቃ መሰረት ቅስቃሰ ጉልበት ወደ ኪሂሎት ጉልበት ከዛ ደግሞ በተቃራኒው ሲመለስ ነው። ዋንኛው ያበረከተው ጠቀሜታ አንድ አካል የሚወድቅበት ቁመት ከ ሚነሳበት ቁመት ጋር እኩል መሆኑን መግለጹ ይህም የ ፍዘትን ጽንሰ ሃሳብ እንዲፈጥር መንገድ ከፍቶለታል። ለላኛው ደግሞ ሰበቃ በሌለበት ቦታ ላይ አንድ አካል የሚነሳበት የ ቁመት መጠን ከ ቦታው ቅርጽ ጋር ግንኙነት አለመኖሩን ማሳየቱ ነው።

በ 1662 ዓ.ም ክርስቲያን ህዩገንስ ፕ ህገ ግጭቱን ጽሁፍ አሳተመ ፤ ይጠበቃሉ ብሎ የ ገለጻቸውም አካላዊ መጠኖች ይ መስመር እንድርድሪት እና ቅስቃሴ ጉልበት ነበሩ። በ ጊዘው በ ልስትክ ግጭት እና በ ኢልስትክ ግጭት መካክከል ያለው ልዩነት ስለማይታወቅ የቱ ዋነኛው ተጠባኢ አካላዊ መጠን ነው በሚል ክርክር አስነስቶ ነበር። ሀሮሎጉም ኦስኪላቶረም በተሰኘው መጻሃፉ የተሻለ ብያኔ ሰጦት ነበር ይህም ከ ዘላለማዊ እንቅስቃሴ አለመቻል ጋር አገናኝቶት ነበር። በ ፐንዱሉም ላይ ያደረገው ጥናት በ ቶርስሌ መርህ መሰረት ነበር የሚለውም የ አንድ ወም ብዙ አካል ማእክላኡ መጠነ ቁስ ራሱን ሊያነሳ አይችልም። በዚህ መርህ መሰረት ህዩገንስ ጉልበትን ብቻ በ መጠቀም (ሃይል እና ጥምዝን ሳይጠቀም) ህጋጋተ ፐንዱለምን ሊፈጥር ችሏል።