Jump to content

ላሾ

ከውክፔዲያ

ላሾ ፣ (በወላይትኛ: Laashsho) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በዎላይታ የሚገኝ ከተማ ነው። ከዎላይታ ሶዶ ከተማ እስከ ላሾ ያለው ግምታዊ ርቀት ወደ ምዕራብ በኩል ኪሎ ሜትር (49 ሚ) ነው። እንዲሁም ከአዲስ አበባ ላሾ ያለው ርቀት 388 ነው። [1] ላሾ ከተማ በዎላይታ ውስጥ የካዎ ኮይሻ ወረዳ የአስተዳደር ዋና ከተማ ሆኖ ያገለግላል። ከተማው ከባህር ጠለል በላይ 2,130 ሜትር ከፍታ ላይ ይገኛል። ላሾ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ ህዝብ ተጠጋግቶ የሚኖርበት ቦታ ነው። በከተማው ያሉት አገልግሎቶች የ24 ሰአት የኤሌክትሪክ መብራት፣ የንፁህ ውሃ አገልግሎት፣ አፀደ ህጻናት፣ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ጣቢያ፣ የእለት ተእለት የህዝብ ገበያ እና ሌሎችም ናቸው። [2] ላሾ በ6°42'29" ሰሜን 37°28'23" ምስራቅ [3] መካከል ይገኛል።