ከ«ጥቅምት ፲፱» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
ጥ «ጥቅምት 19» ወደ «ጥቅምት ፲፱» አዛወረ |
|
(No difference)
|
እትም በ01:19, 25 ጁላይ 2010
ጥቅምት ፲፱ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፵፱ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ቀን በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፫፻፲፯ ቀናት በዮሐንስ፤ በማቴዎስ፤ እና በማርቆስ ዘመናት ደግሞ ፫፻፲፮ ቀናት ይቀራሉ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን የቅዱስ ገብርኤል ዕለት ነው።
ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች
፲፰፻፶፮ ዓ.ም. ጀኔቭ ላይ የተሰበሰቡ የአሥራ ስድስት አገሮች ልዑካን የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ማኅበር ለመመሥረት ተስማሙ። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ተመሥርቶ በ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. የዓለም አቀፋዊው ማኅበር አባል ሆነ። [1]
፲፱፲፭ ዓ.ም. የኢጣልያው ንጉሥ ቪክቶር ኢማኑኤል ሦሥተኛ ለፋሽሽት መሪው ለቤኒቶ ሙሶሊኒ የጠቅላይ ሚኒስቴርነት ሥልጣን ሰጡ።
፲፱፻፲፮ ዓ.ም በአንደኛው የዓለም ጦርነት የተሸነፈውና የተሠባበረው የኦቶማን ግዛት አክትሞ በቦታው የቱርክ ሪፑብሊክ ተመሠረተ።
፲፱፻፵፱ ዓ.ም. በሱዌዝ ሽብር መጀመሪያ የእስራኤል ሠራዊቶች የግብጽን ሠራዊቶች ወደ ሱዌዝ ቦይ በምግፋት የሲናይን በረሐ ማርከው ያዙ።
፲፱፻፶፯ ዓ.ም. በምሥራቅ አፍሪቃ ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋህደው የታንዛኒያ ሕብረት ሪፑብሊክን መሠረቱ።