ከ«የብርሃን ስብረት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
r2.6.4) (ሎሌ መጨመር: kk:Рефракция
r2.7.2) (ሎሌ መጨመር: bn:আলোর প্রতিসরণ
መስመር፡ 16፦ መስመር፡ 16፦
[[be:Праламленне]]
[[be:Праламленне]]
[[bg:Пречупване]]
[[bg:Пречупване]]
[[bn:আলোর প্রতিসরণ]]
[[ca:Refracció]]
[[ca:Refracció]]
[[cs:Lom vlnění]]
[[cs:Lom vlnění]]

እትም በ17:53, 25 ኤፕሪል 2012

ብርሃን ከአየር ወደ ብርጭቆ ስባሪ ሲገባ መሰበሩን የሚያሳይ ምስል። ከብርጭቆው ወደ አየር ሲመለስ አለመሰበሩ፣ የአየሩን ድንበር ገጽታ በቀጤ ነክ ስለሚሰነጥቅ ነው

የብርሃን ስብረት እምንለው የብርሃን ጨረር ካንድ ብርሃን አሳላፊ ወደ ሌላ አሳላፊ አካል ሲጓዝ የሚገጥመውን የመጉበጥ ሁናቴ የሚወክል ጽንስ ሃሳብ ነው። ይህ የመጉበጥ ሁናቴ በስኔል ህግ እንዲህ ሲባል በሒሳብ ቋንቋ ይገለጻል፦

እዚህ ላይ በብርሃኑ ጨረርና በአንደኛው ብርሃን አስተላላፊ አካል ቀጤ ነክ መካከል ያለውን ማዕዘን ሲዎክል ደግሞ በሁለተኛው አካል ቀጤ ነክና በብርሃኑ ጨረር መካከል ያለውን ማዕዘን ይወክላል። n1 እና n2 የብርሃን አስተላላፊዎቹ የስብራት ውድር ናቸው፣ n = 1 ለጠፈር ሲሆን n > 1 ደግሞ ለማናቸው ብርሃን አስተላላፊና በከፊል አስተላላፊ ቁስ አካሎች የሚሆን ነው።

አንድ ጨረር ከአንድ አካል ወጥቶ ወደሌላ አካል ሲገባ የጨረሩ የሞገድ ርዝመትየብርሃን ፍጥነቱ ይቀየራል። ሆኖም ግን ድግግሞሹ ባለበት ይጸናል። ያ ጨረር ለሚገባበት አካል ገላ ቀጤ ነክ ካልሆነ የሞገድ ርዝመቱ ወይም ፍጥነቱ መቀየር ብርሃኑ እንዲጎብጥ ወይም አቅጣጭ እንዲቀይር ያደርገዋል። አንድ መኪና አንድ ጎን ጎማዎቹ ቀጥ ቢሉና ሌሎች ጎን ጎማዎቹ ቢሽከረከሩ ሳይወድ በግድ እንደሚታጠፍ ነው። የብርሃን አቅጣጫ መቀየር የብርሃን ስብረት በመባል ይታወቃል።