ከ«ሀዲስ ዓለማየሁ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
ጥ Robot-assisted disambiguation: እንግሊዝ - Changed link(s) to ዩናይትድ ኪንግደም |
|||
መስመር፡ 12፦ | መስመር፡ 12፦ | ||
*1948-[[1952]] - [[የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት]] የኢትዮጵያ አምባሰደር |
*1948-[[1952]] - [[የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት]] የኢትዮጵያ አምባሰደር |
||
*1952 - የትምህርት ሚኒስትር |
*1952 - የትምህርት ሚኒስትር |
||
*1952-[[1957]] - የኢትዮጵያ አምባሰደር ወደ [[እንግሊዝ]]ና [[ሆላንድ]] |
*1952-[[1957]] - የኢትዮጵያ አምባሰደር ወደ [[ዩናይትድ ኪንግደም|እንግሊዝ]]ና [[ሆላንድ]] |
||
*1957-[[1958]] - የልማት ሚኒስትር |
*1957-[[1958]] - የልማት ሚኒስትር |
||
*[[1960]]-[[1966]] - ሴናቶር |
*[[1960]]-[[1966]] - ሴናቶር |
እትም በ23:06, 26 ኦገስት 2013
ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንጾር ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በጥቅምት ፯ ቀን ፲፱፻፪ ዓ.ም. ተወለዱ። ገና በጨቅላ እድሜያቸው በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት በቤተሰባቸው አጠገብና ባባታቸው አገር ደብረኤልያስ ሄደው የግእዝ ትምሕርት ቤት ቅኔ ተቀኝተዋል። የቤተክርስቲያን ስርዐታትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጎጃም ገዳማት በደብረ ኤልያስ፣ በደብረ ወርቅና በዲማ ከቀሰሙ በኋላ ወደ በ፲፱፻፲፰ ዓ.ም.አዲስ አበባ በመሄድ በስዊድን ሚሽነሪ ትምህርት ቤት በኋላም በራስ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን ተከታተሉ። ለትንሽ ግዜ በአስተማሪነት ሥራ ተሰማርተው እንዳገለገሉ የፋሽስት ጣሊያን ወረራ ተከሰተ።
የኢጣልያ ወረራ ሲከሰት ከልዑል ራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴ ጦር ጋር በምዕራብ ኢትዮጵያ በአርበኝነት ሲዋጉ ቆይተው በመያዛቸው ጣሊያን ከልዑል ራስ እምሩ ጋር በግዞት ለሰባት ዓመት በፖንዞ ደሴትና በሊፓሪ ደሴት ታስረው ቆይተዋል።
ከዚያም የተባባሪ ኃያላት ወታደሮች በ1935 ዓ.ም. ሲያመልጧቸው በተመለሱበት ጊዜ በትምህርታቸው እንደገና በኦክስፎርድ ከገፉ በኋላ በተለያዩ የመንግስት ተቋማት በተለይም በትምህርት ሚኒስቴር ለረጅም ግዜ አገልግለዋል።
- 1936 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሠራተኛ
- 1937-1938 - የኢትዮጵያ ቆንሱል በኢየሩሳሌም
- 1938 - በ International Telecommunications Conference አትላንቲክ ከተማ፣ ኒው ጄርዚ ወኪል
- 1938-1942 - በተባበሩት መንግሥታት ቢሮ ኒው ዮርክ ሠራተኛ
- 1942-1948 - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዳይረክተርና ምክትል
- 1948-1952 - የተባባሩት መንግሥታት ድርጅት የኢትዮጵያ አምባሰደር
- 1952 - የትምህርት ሚኒስትር
- 1952-1957 - የኢትዮጵያ አምባሰደር ወደ እንግሊዝና ሆላንድ
- 1957-1958 - የልማት ሚኒስትር
- 1960-1966 - ሴናቶር
ሀዲስ ዓለማየሁ በርካታ የስነጽሑፍ ሥራዋችን አበርክተዋል። ከነዚህም ውስጥ ታላቅ አድናቆትንና እውቅናን ያተረፈው ሥራቸው ፍቅር እስከ መቃብር (1958) በሁለት የተለያዩ መደቦች ውስጥ የሚገኙ የሁለት ሰዎች የፍቅር ታሪክ ላይ ሲያተኩር፤ በጊዜው የነበረውን ወግና ልማድ ይገልጻል። እንዲሁም በ1970 ወንጀለኛው ዳኛ በ 1980 ደግሞ ስለ ማህበራዊ ጉዳዮችና ስለ ጣሊያን ውርስ የሚዳስሰውን የልም እዣት የተሰኙትን ልብ ወለድ ታሪኮች ለንባብ አቅርባዋል።
ከዚህ ባሻገር:
- የአበሻና የወደኋላ ጋብቻ - ተውኔት
- ተረት ተረት የመሰረት
- ትዝታ
የተሰኙት ጽሁፎችና የሌሎች በርካታ ሥራዎች ባለቤት ናቸው።
ሀዲስ ዓለማየሁ በኢትዮጵያ የስነ ጽሑፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽዖ በማበርከታቸው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክቶርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል። ደራሲው በኅዳር 26 ቀን 1996 ዓ.ም. በ94 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ዋቢ መጻሕፍት
- Historical Dictionary of Ethiopia
- ብሔራዊ ቢብሎግራፊ (የደራሲያን አጭር የሕይወት ታሪክ)፤ (1998 ዓ.ም) ገጽ 13
- ብርሃነ መስቀል ደጀኔ እና ጌታሁን ሽብሩ፤ «ያሠርቱ ምእት፥ የብርዕ ምርት» ፲፱፻፺፱ ዓ.ም.