ከ«ኡሰርካሬ ኸንጀር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
(No difference)
|
እትም በ16:43, 7 ጁን 2014
ኡሰርካሬ ኸንጀር | |
---|---|
በኸንጀር ሀረም ውስጥ የተገኘው የኸንጀር ሀረም ምስል | |
የግብጽ ፈርዖን | |
ግዛት | 1772-1760 ዓክልበ. ግ. |
ቀዳሚ | ኹታዊሬ ወጋፍ |
ተከታይ | ስመንኽካሬ ኢሚረመሻው |
ባለቤት | ሰነብኸናስ |
ሥርወ-መንግሥት | 13ኛው ሥርወ መንግሥት |
ኡሰርካሬ ኸንጀር ላይኛ ግብጽ በ2ኛው ጨለማ ዘመን (13ኛው ሥርወ መንግሥት) ከ1772 እስከ 1760 ዓክልበ. ግድም ድረስ የገዛ ፈርዖን ነበረ። ምናልባት የኹታዊሬ ወጋፍ ተከታይ ነበረ።
በቶሪኖ ቀኖና ነገሥታት ዝርዝር ላይ «ኡሰር<..>ሬ <...>ጀር» ይገኛል። በመምኅር ኪም ራይሆልት አስተሳሰብ፣ «ኸንጀር» የሚለው ስያሜ ግብጽኛ ሳይሆን በአንዳንድ ሴማዊ ቋንቋዎች «እሪያ» ማለት ሊሆን ይችላል። ስለዚህ ሴማዊው ፲፬ኛው ሥርወ መንግሥት በጌሤም እየገዛ ምናልባት የሴማውያን ተጽእኖ በጤቤስ መንግሥት ደግሞ በዚህ ሊታይ ይችላል።
ኸንጀር በተለይ ስላሠራው «የኸንጀር ሀረም» ይታወቃል። በዚህ ሀረም በሁለት ድንጋዮች የኸንጀር ፩ኛው ዓመትና የ፭ኛው ዓመት ዘመነ መንግሥት ተመዘገበ። ስለዚህ ብዙ ሊቃውንት ከ፭ ዓመታት በላይ እንደ ገዛ አያምኑም።
በዚህ ዘመን «ኦሩስ፣ አኸንኸሬስ፣ አኮሪስ፣ ኸንክሬስ፣ አኸሬስ» በግብጽ እንደ ገዙ በአንዳንድ ምንጭ ይገኛል። እነዚህ ስሞች ሆር አዊብሬ፣ ሰኸምሬኹታዊ ኻውባው፣ ሰጀፋካሬ፣ ኸንጀር፣ እና ስመንኽካሬ ቢመስሉም፣ ከማኔጦን ጀምሮ ስሞቻቸው ከ፲፱ኛው ሥርወ መንግሥት ፈርዖኖች ጋር እንደ ተዛቡ ይመስላል። «ኸንክሬስ» የ፲፪ ዓመታት ዘመን እንደ ነበረው ይባላል። በአንዳንድ የድሮ ምንጭ ደግሞ «ኸንክሬስ» በዘጸአት ዘመን የጠፋው ፈርዖን ሲባል ይህ ደግሞ እንደ ተዛበ ይመስላል።
-
የኸንጀር ሀረም ምስል
-
የኸንጀር ስም በአንድ ጽላት ላይ
-
የንግሥት ሰነብኸናስ ጥንዚዛ
ቀዳሚው ኹታዊሬ ወጋፍ |
የግብፅ (ጤቤስ) ፈርዖን 1772-1760 ዓክልበ. ግድም |
ተከታይ ስመንኽካሬ ኢሚረመሻው |
ዋቢ ምንጭ
- K.S.B. Ryholt: The Political Situation in Egypt during the Second Intermediate Period, c. 1800 – 1550 BC, Carsten Niebuhr Institute Publications, vol. 20. Copenhagen: Museum Tusculanum Press, 1997 (እንግሊዝኛ)