ከ«ካሩም» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 6፦ መስመር፡ 6፦
ከዚህ ጥቂት ዓመታት በኋላ የ[[አካድ]] ንጉሥ [[ታላቁ ሳርጎን]] ኤብላን አጠፋ። ከኋለኛ ዘመን በ[[ኬጥኛ]] በተጻፈ ታሪክ ዘንድ፣ የ[[ቡሩሻንዳ]] ንጉሥ ኑርዳጋል በ''ካሩሞች'' የነበሩትን አካዳዊና አሦራዊ ነጋዴዎች መደብ ስለ በደለ፣ ሳርጎን ደግሞ አናቶሊያን ወረረ። ይህም ድርሰት በ[[አማርና ደብዳቤዎች]] መካከል በ[[አካድኛ]] ተገኘ፤ ቅጂዎቹ ግን በሳርጎን ዘመን ስላልተጻፉ እንደ ታማኝ ታሪክ አይቆጠሩም።
ከዚህ ጥቂት ዓመታት በኋላ የ[[አካድ]] ንጉሥ [[ታላቁ ሳርጎን]] ኤብላን አጠፋ። ከኋለኛ ዘመን በ[[ኬጥኛ]] በተጻፈ ታሪክ ዘንድ፣ የ[[ቡሩሻንዳ]] ንጉሥ ኑርዳጋል በ''ካሩሞች'' የነበሩትን አካዳዊና አሦራዊ ነጋዴዎች መደብ ስለ በደለ፣ ሳርጎን ደግሞ አናቶሊያን ወረረ። ይህም ድርሰት በ[[አማርና ደብዳቤዎች]] መካከል በ[[አካድኛ]] ተገኘ፤ ቅጂዎቹ ግን በሳርጎን ዘመን ስላልተጻፉ እንደ ታማኝ ታሪክ አይቆጠሩም።


በሐቲ እነዚህ የአሦራውያን ነጋዴ ሠፈሮች ከሐቲ ከተሞች አጠገብ ይመሠረት ነበር፤ ቀረጥም ለከተማው ገዢ ያስረክቡ ነበር።<ref>Seton Lloyd : ''Ancient Turkey'' ( Translation: Ender Verinlioğlu) Tubitak, Ankara, 1998 p 18-19</ref> አነስተኛ «መባርቱም» የተባሉት ጣቢያዎች ደግሞ ነበሯቸው። በተለይ 1880-1750 እና 1720-1680 ዓክልበ. በጠቅላላ የ''ካሩም''ና የ''መባርቱም'' ቁጥር ምናልባት ፳ ያሕል ነበር። ከነዚህም ውስጥ [[ካነሽ]]፣ [[አንኩቫ]]፣ [[ሐቱሳሽ]] በዋናነት ይጠቀሳሉ። [[የኬጥያውያን መንግሥት]] ከተነሣ ቀጥሎ ግን ''ካሩሞቹ'' ከአናቶሊያ ጠፉ።
በሐቲ እነዚህ የአሦራውያን ነጋዴ ሠፈሮች ከሐቲ ከተሞች አጠገብ ይመሠረቱ ነበር፤ ቀረጥም ለከተማው ገዢ ያስረክቡ ነበር።<ref>Seton Lloyd : ''Ancient Turkey'' ( Translation: Ender Verinlioğlu) Tubitak, Ankara, 1998 p 18-19</ref> አነስተኛ «መባርቱም» የተባሉት ጣቢያዎች ደግሞ ነበሯቸው። በተለይ 1880-1750 እና 1720-1680 ዓክልበ. በጠቅላላ የ''ካሩም''ና የ''መባርቱም'' ቁጥር ምናልባት ፳ ያሕል ነበር። ከነዚህም ውስጥ [[ካነሽ]]፣ [[አንኩቫ]]፣ [[ሐቱሳሽ]] በዋናነት ይጠቀሳሉ። [[የኬጥያውያን መንግሥት]] ከተነሣ ቀጥሎ ግን ''ካሩሞቹ'' ከአናቶሊያ ጠፉ።


በዚሁ ዘመን መደበኛ ገንዘብ (መሀልቅ) ገና አልተፈጠረም ነበር። የአሦር ነጋዴዎች [[ወርቅ]] በጅምላ፣ [[ብር (ብረታብረት)|ብር]] ለችርቻሮ ይጠቅማቸው ነበር። የወርቅ ዋጋ ከብር ፰ እጥፍ መሆኑ ተወሰነ። ሆኖም ሌላ የብረታብረት አይነት በአሦርኛ «አሙቱም» ሲባል ይህ ከወርቅም በላይ ውድ ነበር፤ ከብር ፵ ጊዜ ተላቀ። «አሙቱም» ምናልባት ያንጊዜ ትኩስ ግኝት የነበረ [[ብረት]] ሊሆን ይቻላል። እነዚህ የአሦር ነጋዴዎች በተለይም [[ቆርቆሮ]]ና [[ልብስ]] ለሐቲ ሰዎች ይሸጡ ነበር። ከሐቲ አገር ካስወጡአቸው ውጤቶች መካከል ከሁሉ አይነተኛ የሆነው [[መዳብ]] ነበረ።<ref>Ekrem Akurgal: ''Anadolu Kültür Tarihi'',Tubitak, Ankara,2000 ISBN 975-403-107-X p 40-41</ref>
በዚሁ ዘመን መደበኛ ገንዘብ (መሀልቅ) ገና አልተፈጠረም ነበር። የአሦር ነጋዴዎች [[ወርቅ]] በጅምላ፣ [[ብር (ብረታብረት)|ብር]] ለችርቻሮ ይጠቅማቸው ነበር። የወርቅ ዋጋ ከብር ፰ እጥፍ መሆኑ ተወሰነ። ሆኖም ሌላ የብረታብረት አይነት በአሦርኛ «አሙቱም» ሲባል ይህ ከወርቅም በላይ ውድ ነበር፤ ከብር ፵ ጊዜ ተላቀ። «አሙቱም» ምናልባት ያንጊዜ ትኩስ ግኝት የነበረ [[ብረት]] ሊሆን ይቻላል። እነዚህ የአሦር ነጋዴዎች በተለይም [[ቆርቆሮ]]ና [[ልብስ]] ለሐቲ ሰዎች ይሸጡ ነበር። ከሐቲ አገር ካስወጡአቸው ውጤቶች መካከል ከሁሉ አይነተኛ የሆነው [[መዳብ]] ነበረ።<ref>Ekrem Akurgal: ''Anadolu Kültür Tarihi'',Tubitak, Ankara,2000 ISBN 975-403-107-X p 40-41</ref>

እትም በ22:48, 9 ጁላይ 2014

መካከለኛ አናቶሊያ

ካሩም በጥንት (2150-1680 ዓክልበ. ያሕል) የአሦር ሰዎች በውጭ አገራት በተለይ በሐቲ (አናቶሊያ) ያቋቋሙት የንግድ ሠፈሮች ነበሩ።

ኤብላ ጽላቶች መካከል አንዱ ሰነድ ከኤብላ (በሶርያ) እና ከአሹር (ወይም ከአባርሳል?) መካከል የተዋወለ ውል ሲሆን በዚህ ውል አሹር በኤብላ ግዛት ውስጥ ካሩም ለማስተዳደር ፈቃድ አገኘ።

ከዚህ ጥቂት ዓመታት በኋላ የአካድ ንጉሥ ታላቁ ሳርጎን ኤብላን አጠፋ። ከኋለኛ ዘመን በኬጥኛ በተጻፈ ታሪክ ዘንድ፣ የቡሩሻንዳ ንጉሥ ኑርዳጋል በካሩሞች የነበሩትን አካዳዊና አሦራዊ ነጋዴዎች መደብ ስለ በደለ፣ ሳርጎን ደግሞ አናቶሊያን ወረረ። ይህም ድርሰት በአማርና ደብዳቤዎች መካከል በአካድኛ ተገኘ፤ ቅጂዎቹ ግን በሳርጎን ዘመን ስላልተጻፉ እንደ ታማኝ ታሪክ አይቆጠሩም።

በሐቲ እነዚህ የአሦራውያን ነጋዴ ሠፈሮች ከሐቲ ከተሞች አጠገብ ይመሠረቱ ነበር፤ ቀረጥም ለከተማው ገዢ ያስረክቡ ነበር።[1] አነስተኛ «መባርቱም» የተባሉት ጣቢያዎች ደግሞ ነበሯቸው። በተለይ 1880-1750 እና 1720-1680 ዓክልበ. በጠቅላላ የካሩምና የመባርቱም ቁጥር ምናልባት ፳ ያሕል ነበር። ከነዚህም ውስጥ ካነሽአንኩቫሐቱሳሽ በዋናነት ይጠቀሳሉ። የኬጥያውያን መንግሥት ከተነሣ ቀጥሎ ግን ካሩሞቹ ከአናቶሊያ ጠፉ።

በዚሁ ዘመን መደበኛ ገንዘብ (መሀልቅ) ገና አልተፈጠረም ነበር። የአሦር ነጋዴዎች ወርቅ በጅምላ፣ ብር ለችርቻሮ ይጠቅማቸው ነበር። የወርቅ ዋጋ ከብር ፰ እጥፍ መሆኑ ተወሰነ። ሆኖም ሌላ የብረታብረት አይነት በአሦርኛ «አሙቱም» ሲባል ይህ ከወርቅም በላይ ውድ ነበር፤ ከብር ፵ ጊዜ ተላቀ። «አሙቱም» ምናልባት ያንጊዜ ትኩስ ግኝት የነበረ ብረት ሊሆን ይቻላል። እነዚህ የአሦር ነጋዴዎች በተለይም ቆርቆሮልብስ ለሐቲ ሰዎች ይሸጡ ነበር። ከሐቲ አገር ካስወጡአቸው ውጤቶች መካከል ከሁሉ አይነተኛ የሆነው መዳብ ነበረ።[2]

ዋቢ ምንጮች

  1. ^ Seton Lloyd : Ancient Turkey ( Translation: Ender Verinlioğlu) Tubitak, Ankara, 1998 p 18-19
  2. ^ Ekrem Akurgal: Anadolu Kültür Tarihi,Tubitak, Ankara,2000 ISBN 975-403-107-X p 40-41