ከ«መጥምቁ ዮሐንስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «350px|thumb|ዮሐንስ በ1500 ዓም ያህል በጀርመን እንደ ተሳለ '''መጥምቁ ዮሐን...»
 
No edit summary
መስመር፡ 2፦ መስመር፡ 2፦
'''መጥምቁ ዮሐንስ''' በ[[ወንጌላት]] እንደ ተገለጸ በ[[ኢየሱስ]] ወቅት በ[[ይሁዳ]] የተመላለሰ ሰባኪ ነበር። በ[[ክርስትና]]፣ እንዲሁም በ[[እስልምና]]፣ በ[[ባኃኢ እምነት]] እና በ[[ማንዳይስም]] እንደ ነቢይ ይቆጠራል።
'''መጥምቁ ዮሐንስ''' በ[[ወንጌላት]] እንደ ተገለጸ በ[[ኢየሱስ]] ወቅት በ[[ይሁዳ]] የተመላለሰ ሰባኪ ነበር። በ[[ክርስትና]]፣ እንዲሁም በ[[እስልምና]]፣ በ[[ባኃኢ እምነት]] እና በ[[ማንዳይስም]] እንደ ነቢይ ይቆጠራል።


አባቱ [[ዘካርያስ (የመጥምቁ ዮሐንስ አባት)|ዘካርያስ]]ና እናቱ [[ኤልሳቤት]] ነበሩ። በ[[አዲስ ኪዳን]] መሠረት፣ ዮሕንስ በይሁዳ ምድረ በዳ ሲዛወር የ[[ግመል]] ጽጉር ልብስና የቆዳ ቀለብቶ ለብሶ መብሉ [[አንበጣ]]ና [[ማር]] ነበረ። [[ንስሐ]] መግባት እና ለ[[መሲኅ]] መንግሥት መዘጋጀት ይሰብክ ነበር። ብዙ ሕዝብ ከ[[ኢየሩሳሌም]]ና ከይሁዳ ሄደው ሰምተው በ[[ዮርዳኖስ ወንዝ]] ተጠመቁ። የ[[ፈሪሳውያን]]ና [[ሰዱቃውያን]] ወገኖች ግን ገሰጻቸው። [[አይሁድ]] መሆን ወይም ከ[[አብርሃም]] መወለድ ብቻ ለ[[እግዚአብሔር]] መንግሥት ለመዳን በቂ እንዳልነበረ ነገራቸው።
አባቱ [[ዘካርያስ (የመጥምቁ ዮሐንስ አባት)|ዘካርያስ]]ና እናቱ [[ኤልሳቤት]] ነበሩ። በ[[አዲስ ኪዳን]] መሠረት፣ ዮሐንስ በይሁዳ ምድረ በዳ ሲዛወር የ[[ግመል]] ጽጉር ልብስና የቆዳ ቀለብቶ ለብሶ መብሉ [[አንበጣ]]ና [[ማር]] ነበረ። [[ንስሐ]] መግባት እና ለ[[መሲኅ]] መንግሥት መዘጋጀት ይሰብክ ነበር። ብዙ ሕዝብ ከ[[ኢየሩሳሌም]]ና ከይሁዳ ሄደው ሰምተው በ[[ዮርዳኖስ ወንዝ]] ተጠመቁ። የ[[ፈሪሳውያን]]ና [[ሰዱቃውያን]] ወገኖች ግን ገሰጻቸው። [[አይሁድ]] መሆን ወይም ከ[[አብርሃም]] መወለድ ብቻ ለ[[እግዚአብሔር]] መንግሥት ለመዳን በቂ እንዳልነበረ ነገራቸው።


በተለይ በ[[ሉቃስ ወንጌል]] ከተዘረዘሩት ትምህርቶቹ፦
በተለይ በ[[ሉቃስ ወንጌል]] ከተዘረዘሩት ትምህርቶቹ፦

እትም በ17:41, 26 ኤፕሪል 2017

ዮሐንስ በ1500 ዓም ያህል በጀርመን እንደ ተሳለ

መጥምቁ ዮሐንስወንጌላት እንደ ተገለጸ በኢየሱስ ወቅት በይሁዳ የተመላለሰ ሰባኪ ነበር። በክርስትና፣ እንዲሁም በእስልምና፣ በባኃኢ እምነት እና በማንዳይስም እንደ ነቢይ ይቆጠራል።

አባቱ ዘካርያስና እናቱ ኤልሳቤት ነበሩ። በአዲስ ኪዳን መሠረት፣ ዮሐንስ በይሁዳ ምድረ በዳ ሲዛወር የግመል ጽጉር ልብስና የቆዳ ቀለብቶ ለብሶ መብሉ አንበጣማር ነበረ። ንስሐ መግባት እና ለመሲኅ መንግሥት መዘጋጀት ይሰብክ ነበር። ብዙ ሕዝብ ከኢየሩሳሌምና ከይሁዳ ሄደው ሰምተው በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቁ። የፈሪሳውያንሰዱቃውያን ወገኖች ግን ገሰጻቸው። አይሁድ መሆን ወይም ከአብርሃም መወለድ ብቻ ለእግዚአብሔር መንግሥት ለመዳን በቂ እንዳልነበረ ነገራቸው።

በተለይ በሉቃስ ወንጌል ከተዘረዘሩት ትምህርቶቹ፦

  • ለሕዝቡ፦ «ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፣ ምግብም ያለው እንዲህ ያድርግ»
  • ለቀራጮች፦ «ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ»
  • ለጭፍሮች (ለወታደሮች)፦ «በማንም ግፍ አትሥሩ፣ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፣ ደመወዛችሁም ይብቃችሁ።»

ስለ ዮሐንስ ቅድስና አንዳንድ ሰዎች መሲህ እራሱ እንደ ነበር ያስቡ ነበር፤ ዮሐንስ ግን ከኔ ይልቅ የሆነ ሊመጣ ነው ብሎ ነበየ።

ኢየሱስ ደግሞ ወደ ዮሐንስ ለጥምቀት ሲቀርብ፣ የእግዚአብሔር ድምጽና መንፈስ እንደ ዋኖስ ወርዶ ይህ ልጄ ነው አለ። ዮሐንስ በመንፈሱ ኢየሱስ መሲኅ እንደ ነበር ዓወቀ።

በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት እየሠራ ዮሐንስ ተከታዮቹን ወደ ኢየሱስ ልኮ የምንጠብቀው መሲኅ ይህ ነው ወይ ብለው ጠየቁት። ተዓምራት መሥራቴን ንገረው ብሎ መለሳቸው። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ ገልጾ በትንቢተ ሚልክያስ እንደ ተነበየ የሚመጣው ኤልያስ ነው በማለት አስተማረ። ሆኖም ዮሐንስ እራሱ ኤልያስ አይደለሁም ስላለ፣ ሉቃስ እንደ ጻፈው በኤልያስ ኃይልና መንፈስ እንደ ተወለደ እንጂ የኤልያስ ነፍስ ትስብዕት ተመልሶ መሆኑ አይታመንም።

ዮሐንስ ደግሞ የሮሜ መንግሥት ደንበኛ-ንጉሥ ሄሮድያስን ገሰጸው። ሄሮድያስ የወንድሙን ሚስት ማግባቱ በሕገ ሙሴ ዘንድ ሕገ ወጥ መሆኑን አሳወቀው። ስለዚህ መቀያየም ሄሮድያስ ዮሐንስን በወህኒ አሠረው በኋላም ራሱን አስቆረጠው።

ከዚያ ትንሽ በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት ስለ መሥራቱ ዝነኛ ሲሆን፣ ሄሮድያስ እንደ መሰለው ዮሐንስ በትንሳኤ ተመልሷል ብሎ ገመተ። ሌሎችም ኢየሱስ እንደ ኤልያስ በትንሳኤ ተመልሷል ብለው ያስቡ ነበር።

የዮሐንስ ተከታዮች ብዙ ጊዜ ይጾሙ ነበር፤ ብዙዎቹም የኢየሱስ ተከታዮች ሆኑ። ኤብዮናውያን የተባለው ወገን አትክልት ብቻ ሲበሉ ዮሐንስ ስንኳ አንበጣ አልበላም ያምኑ ነበር።

ዮሴፉስ

የአይሁድ ታሪክ ጸሐፊ ፍላቪዩስ ዮሴፉስ (70 ዓም ግ.) እንዳለን፣ ሄሮድያስ ዮሐንስን በወህኒ ስላስገደለው፣ ከዚህ እርጉም የተነሣ ከ፮ ዓመታት በኋላ በ28 ዓም የሄሮድያስ ሥራዊት ተሸነፈ።

ማንዳይስም

ማንዳይስም በኢራቅ የተገኘ አነስተኛ የኖስቲሲስም አይነት እምነት ሲሆን፣ ዮሐንስ እንደ ዋና ነቢያቸው እና መሲኃቸው ይቆጥሩታል፤ ኢየሱስን ግን አይቀበሉም።

እስልምና

በቁራን ዘንድ ስሙ «የህየ» ሲሆን ጽድቅ ነቢይና የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ይባላል። በሃዲስ ልማዶች መሠረት ደግሞ በ613 ዓም ነቢዩ ሙሐመድ ወደ ሰማይ ተጉዞ በዚያ የህየንንና ኢየሱስን እንዳገኛቸው ይታመናል።

ሞርሞኒስም

በሞርሞኒስም ዘንድ ዮሐንስ በትንሳኤ ለመሥራቹ ለጆሰፍ ስሚስ1821 ዓም በፔንስልቫኒያ ታየው።

ባኃኢ እምነት

በባኃኢ እምነት የእምነቱ መሥራች ባኃኡላህ ቀዳሚ ባብ በነቢዩ ዮሐንስ መንፈስ እንደ ተላከ ይታመናል።

: