ከ«መጥምቁ ዮሐንስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 16፦ መስመር፡ 16፦
በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት እየሠራ ዮሐንስ ተከታዮቹን ወደ ኢየሱስ ልኮ የምንጠብቀው መሲኅ ይህ ነው ወይ ብለው ጠየቁት። ተዓምራት መሥራቴን ንገረው ብሎ መለሳቸው። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ ገልጾ በ[[ትንቢተ ሚልክያስ]] እንደ ተነበየ የሚመጣው [[ኤልያስ]] ነው በማለት አስተማረ (ማቴ. ፲፩)። ሆኖም ዮሐንስ እራሱ ኤልያስ አይደለሁም ስላለ (ዮሐ ፩)፣ ሉቃስ ፩ እንደ ጻፈው በኤልያስ ኃይልና መንፈስ እንደ ተወለደ እንጂ የኤልያስ ነፍስ ትስብዕት ተመልሶ መሆኑ አይታመንም።
በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት እየሠራ ዮሐንስ ተከታዮቹን ወደ ኢየሱስ ልኮ የምንጠብቀው መሲኅ ይህ ነው ወይ ብለው ጠየቁት። ተዓምራት መሥራቴን ንገረው ብሎ መለሳቸው። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ ገልጾ በ[[ትንቢተ ሚልክያስ]] እንደ ተነበየ የሚመጣው [[ኤልያስ]] ነው በማለት አስተማረ (ማቴ. ፲፩)። ሆኖም ዮሐንስ እራሱ ኤልያስ አይደለሁም ስላለ (ዮሐ ፩)፣ ሉቃስ ፩ እንደ ጻፈው በኤልያስ ኃይልና መንፈስ እንደ ተወለደ እንጂ የኤልያስ ነፍስ ትስብዕት ተመልሶ መሆኑ አይታመንም።


ዮሐንስ ደግሞ [[የሮሜ መንግሥት]] ደንበኛ-ንጉሥ [[ሄሮድያስ]]ን ገሰጸው። ሄሮድያስ የወንድሙን ሚስት ማግባቱ በ[[ሕገ ሙሴ]] ዘንድ ሕገ ወጥ መሆኑን አሳወቀው። ስለዚህ መቀያየም ሄሮድያስ ዮሐንስን በወህኒ አሠረው በኋላም ራሱን አስቆረጠው።
ዮሐንስ ደግሞ [[የሮሜ መንግሥት]] ደንበኛ-ንጉሥ [[ሄሮድያስ]]ን ገሰጸው። ሄሮድያስ የወንድሙን ሚስት ማግባቱ በ[[ሕገ ሙሴ]] ዘንድ ሕገ ወጥ መሆኑን አሳወቀው። ስለዚህ መቀያየም ሄሮድያስ ዮሐንስን በወህኒ አሠረው በኋላም በሴት ልጁ በ[[ሄሮድያዳ]] ምክር ራሱን አስቆረጠው።


ከዚያ ትንሽ በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት ስለ መሥራቱ ዝነኛ ሲሆን፣ ሄሮድያስ እንደ መሰለው ዮሐንስ በትንሳኤ ተመልሷል ብሎ ገመተ። ሌሎችም ኢየሱስ እንደ ኤልያስ በትንሳኤ ተመልሷል ብለው ያስቡ ነበር (ማር. ፮፣ ማቴ. ፲፬)።
ከዚያ ትንሽ በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት ስለ መሥራቱ ዝነኛ ሲሆን፣ ሄሮድያስ እንደ መሰለው ዮሐንስ በትንሳኤ ተመልሷል ብሎ ገመተ። ሌሎችም ኢየሱስ እንደ ኤልያስ በትንሳኤ ተመልሷል ብለው ያስቡ ነበር (ማር. ፮፣ ማቴ. ፲፬)።

እትም በ21:54, 26 ኤፕሪል 2017

ዮሐንስ በ1500 ዓም ያህል በጀርመን እንደ ተሳለ

መጥምቁ ዮሐንስወንጌላት እንደ ተገለጸ በኢየሱስ ወቅት በይሁዳ የተመላለሰ ሰባኪ ነበር። በክርስትና፣ እንዲሁም በእስልምና፣ በባኃኢ እምነት እና በማንዳይስም እንደ ነቢይ ይቆጠራል።

አባቱ ዘካርያስና እናቱ ኤልሳቤት ነበሩ። በአዲስ ኪዳን መሠረት፣ ዮሐንስ በይሁዳ ምድረ በዳ ሲዛወር የግመል ጽጉር ልብስና የቆዳ ቀለብቶ ለብሶ መብሉ አንበጣማር ነበረ። ንስሐ መግባት እና ለመሲኅ መንግሥት መዘጋጀት ይሰብክ ነበር። ብዙ ሕዝብ ከኢየሩሳሌምና ከይሁዳ ሄደው ሰምተው በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቁ። የፈሪሳውያንሰዱቃውያን ወገኖች ግን ገሰጻቸው። የአይሁድ ዘር መሆን ወይም ከአብርሃም መወለድ ብቻ ለእግዚአብሔር መንግሥት ለመዳን በቂ እንዳልነበረ ነገራቸው (ማቴ.፫፣ ሉቃ ፫)።

በተለይ በሉቃስ ወንጌል ፫ ከተዘረዘሩት ትምህርቶቹ፦

  • ለሕዝቡ፦ «ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፣ ምግብም ያለው እንዲህ ያድርግ»
  • ለቀራጮች፦ «ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ»
  • ለጭፍሮች (ለወታደሮች)፦ «በማንም ግፍ አትሥሩ፣ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፣ ደመወዛችሁም ይብቃችሁ።»

ስለ ዮሐንስ ቅድስና አንዳንድ ሰዎች መሲህ እራሱ እንደ ነበር ያስቡ ነበር፤ ዮሐንስ ግን ከኔ ይልቅ የሆነ ሊመጣ ነው ብሎ ነበየ።

ኢየሱስ ደግሞ ወደ ዮሐንስ ለጥምቀት ሲቀርብ፣ የእግዚአብሔር ድምጽና መንፈስ እንደ ዋኖስ ወርዶ ይህ ልጄ ነው አለ። ዮሐንስ በመንፈሱ ኢየሱስ መሲኅ እንደ ነበር ዓወቀ።

በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት እየሠራ ዮሐንስ ተከታዮቹን ወደ ኢየሱስ ልኮ የምንጠብቀው መሲኅ ይህ ነው ወይ ብለው ጠየቁት። ተዓምራት መሥራቴን ንገረው ብሎ መለሳቸው። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ ገልጾ በትንቢተ ሚልክያስ እንደ ተነበየ የሚመጣው ኤልያስ ነው በማለት አስተማረ (ማቴ. ፲፩)። ሆኖም ዮሐንስ እራሱ ኤልያስ አይደለሁም ስላለ (ዮሐ ፩)፣ ሉቃስ ፩ እንደ ጻፈው በኤልያስ ኃይልና መንፈስ እንደ ተወለደ እንጂ የኤልያስ ነፍስ ትስብዕት ተመልሶ መሆኑ አይታመንም።

ዮሐንስ ደግሞ የሮሜ መንግሥት ደንበኛ-ንጉሥ ሄሮድያስን ገሰጸው። ሄሮድያስ የወንድሙን ሚስት ማግባቱ በሕገ ሙሴ ዘንድ ሕገ ወጥ መሆኑን አሳወቀው። ስለዚህ መቀያየም ሄሮድያስ ዮሐንስን በወህኒ አሠረው በኋላም በሴት ልጁ በሄሮድያዳ ምክር ራሱን አስቆረጠው።

ከዚያ ትንሽ በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት ስለ መሥራቱ ዝነኛ ሲሆን፣ ሄሮድያስ እንደ መሰለው ዮሐንስ በትንሳኤ ተመልሷል ብሎ ገመተ። ሌሎችም ኢየሱስ እንደ ኤልያስ በትንሳኤ ተመልሷል ብለው ያስቡ ነበር (ማር. ፮፣ ማቴ. ፲፬)።

የዮሐንስ ተከታዮች ብዙ ጊዜ ይጾሙ ነበር (ሉቃ. ፭)፤ ብዙዎቹም በኋላ ከአፖሎስ ጋር የኢየሱስ ተከታዮች ሆኑ (የሐዋርያት ሥራ ፲፰፣ ፲፱)። ኤብዮናውያን የተባለው ወገን አትክልት ብቻ ሲበሉ ዮሐንስ ስንኳ አንበጣ አልበላም ያምኑ ነበር፤ የኤብዮናውያን ወንጌል እንዳለው የበላው «የማር እንጐቻ» ነበር።

ዮሴፉስ

የአይሁድ ታሪክ ጸሐፊ ፍላቪዩስ ዮሴፉስ (70 ዓም ግ.) እንዳለን፣ ሄሮድያስ የተከታዮቹን ብዛት ፈርቶ ዮሐንስን በወህኒ ስላስገደለው፣ ከዚህ እርጉም የተነሣ ከ፮ ዓመታት በኋላ በ28 ዓም የሄሮድያስ ሥራዊት በውግያ ተሸነፈ።

ማንዳይስም

ማንዳይስም በኢራቅ የተገኘ አነስተኛ የኖስቲሲስም አይነት እምነት ሲሆን፣ ዮሐንስ እንደ ዋና ነቢያቸው እና መሲኃቸው ይቆጥሩታል፤ ኢየሱስን ግን አይቀበሉም።

እስልምና

ቁራን ዘንድ ስሙ «የህየ» ሲሆን ጽድቅ ነቢይና የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ይባላል። በሃዲስ ልማዶች መሠረት ደግሞ በ613 ዓም ነቢዩ ሙሐመድ ወደ ሰማይ ተጉዞ በዚያ የህየንና ኢየሱስን እንዳገኛቸው ይታመናል።

ሞርሞኒስም

ሞርሞኒስም ዘንድ ዮሐንስ በትንሳኤ ለመሥራቹ ለጆሰፍ ስሚስ1821 ዓም በፔንስልቫኒያ ታየው።

ባኃኢ እምነት

በባኃኢ እምነት የእምነቱ መሥራች የባኃኡላህ ቀዳሚ ባብ (1812-1842 ዓም.) በነቢዩ ዮሐንስ እንዲሁም በኤልያስ መንፈስ እንደ ተላከ ይታመናል።

: