ከ«የማቴዎስ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1፦ መስመር፡ 1፦
{{infobox|abovestyle=background:#FFD300|above=ቅዱስ ማቴዎስ|image=[[File:Matthew the Evangelist.jpg ]]|caption=|headerstyle=background:#FFD300|header1= የማቴዎስ ወንጌል|headerstyle=background:#FFD300|header10=<span style="color:#FFD300">
{{infobox|abovestyle=background:#FFD300|above=ቅዱስ ማቴዎስ|image=[[File:Matthew the Evangelist.jpg ]]|caption=|headerstyle=background:#FFD300|header1= የማቴዎስ ወንጌል|headerstyle=background:#FFD300|header10=<span style="color:#FFD300">
</span>|label1=|data1=|label2=የተወለደው|data2=በ፩ኛው ዓ.ም. በ[[ቀፈርናሆም]]  |label3=ሥራው|data3=መጀመሪያ የ[[ሮማ መንግሥት]] ግብር ሰብሳቢ በኋላ የ[[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ደቀመዝሙር ፣ ሰባኪ ፣ ፀሐፊ |label4=የአባት ስም|data4=አልፍዮስ|label5= የታወቀ ቤ/ክርስቲያን|data5=[[:en:Salerno|ሳሌርኖ]]፣[[ጣሊያን]]|label6=ያረፈበት ቀን|data6=[[ኅዳር ፰]] ሂራፖሊስ አካባቢ ወይም [[ኢትዮጵያ]]|label7=ንግሥና ምልክት|data7=[[ኅዳር ፰]] መልዐክ[[File:Kápolnásnyék pulpit Matthew.jpg|88px]]|label8=የሚከበረው|data8=በመላው [[ክርስትና]] ሃይማኖት ተከታይ |label9=የጻፈው ወንጌል|data9=፳፰ ምዕራፍ|captionstyle=|header5=}}'''የጌታችን የ[[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ወንጌል ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው''' ። ከአራቱ ወንጌላት አንደኛው ነው። በ[[መጽሐፍ ቅዱስ]] [[አዲስ ኪዳን]] ውስጥ ከሁሉ በፊት ይገኛል። በዕብራይስጥና በአርማይስጥ ቋንቋ ማቴዎስ ማለት ሀብተ አምላክ ወይም የአምላክ ስጦታ ማለት እንደሆነ ይነገራል ። በአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የስም ዝርዝር ውስጥ በሁለተኛውና በሦስተኛው ማለትም በማርቆስና በሉቃስ ወንጌል በተራ ቁጥር ሰባተኛ ሲሆን ስሙም ማቴዎስ በመባል ተመዝግቦአል (ማር.፫:፲፮-፲፱ ፡ ሉቃ.፮:፲፬-፲፮) ።
</span>|label1=|data1=|label2=የተወለደው|data2=በ፩ኛው ዓ.ም. በ[[ቀፈርናሆም]]  |label3=ሥራው|data3=መጀመሪያ የ[[ሮማ መንግሥት]] ግብር ሰብሳቢ በኋላ የ[[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ደቀመዝሙር ፣ ሰባኪ ፣ ፀሐፊ |label4=የአባት ስም|data4=አልፍዮስ|label5= የታወቀ ቤ/ክርስቲያን|data5=[[:en:Salerno|ሳሌርኖ]]፣[[ጣሊያን]]|label6=ያረፈበት ቀን|data6=[[ኅዳር ፰]] ሂራፖሊስ አካባቢ ወይም [[ኢትዮጵያ]]|label7=ንግሥና ምልክት|data7=[[ኅዳር ፰]] መልዐክ[[File:Kápolnásnyék pulpit Matthew.jpg|88px]]|label8=የሚከበረው|data8=በመላው [[ክርስትና]] ሃይማኖት ተከታይ |label9=የጻፈው [[ወንጌል]]|data9=፳፰ ምዕራፍ|captionstyle=|header5=}}'''የጌታችን የ[[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ወንጌል ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው''' ። ከአራቱ ወንጌላት አንደኛው ነው። በ[[መጽሐፍ ቅዱስ]] [[አዲስ ኪዳን]] ውስጥ ከሁሉ በፊት ይገኛል። በዕብራይስጥና በአርማይስጥ ቋንቋ ማቴዎስ ማለት ሀብተ አምላክ ወይም የአምላክ ስጦታ ማለት እንደሆነ ይነገራል ። በአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የስም ዝርዝር ውስጥ በሁለተኛውና በሦስተኛው ማለትም በማርቆስና በሉቃስ ወንጌል በተራ ቁጥር ሰባተኛ ሲሆን ስሙም ማቴዎስ በመባል ተመዝግቦአል (ማር.፫:፲፮-፲፱ ፡ ሉቃ.፮:፲፬-፲፮) ።


ራሱ በጻፈው ወንጌልና በሐዋርያት ሥራ ደግሞ በተራ ቁጥር ስምንተኛ ሆኖ ማቴዎስ በመባል ተመዝግቦአል (ማቴ.፲: ፪-፬ ፡ የሐ.ሥ.፩-፲፫) ሌዊ ለሐዋርያነት ከመመረጡ በፊት የተጠራበት ስሙ ሲሆን ማቴዎስ ደግሞ ለወንጌል አገልግሎት በሐዋርያነት ከተጠራ በኋላ የተጠራበት ስሙ ነው ።
ራሱ በጻፈው ወንጌልና በሐዋርያት ሥራ ደግሞ በተራ ቁጥር ስምንተኛ ሆኖ ማቴዎስ በመባል ተመዝግቦአል (ማቴ.፲: ፪-፬ ፡ የሐ.ሥ.፩-፲፫) ሌዊ ለሐዋርያነት ከመመረጡ በፊት የተጠራበት ስሙ ሲሆን ማቴዎስ ደግሞ ለወንጌል አገልግሎት በሐዋርያነት ከተጠራ በኋላ የተጠራበት ስሙ ነው ።

እትም በ06:55, 8 ፌብሩዌሪ 2019

ቅዱስ ማቴዎስ
የማቴዎስ ወንጌል
የተወለደው በ፩ኛው ዓ.ም. በቀፈርናሆም 
ሥራው መጀመሪያ የሮማ መንግሥት ግብር ሰብሳቢ በኋላ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዝሙር ፣ ሰባኪ ፣ ፀሐፊ
የአባት ስም አልፍዮስ
የታወቀ ቤ/ክርስቲያን ሳሌርኖጣሊያን
ያረፈበት ቀን ኅዳር ፰ ሂራፖሊስ አካባቢ ወይም ኢትዮጵያ
ንግሥና ምልክት ኅዳር ፰ መልዐክ
የሚከበረው በመላው ክርስትና ሃይማኖት ተከታይ
የጻፈው ወንጌል ፳፰ ምዕራፍ

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ጻፈው ። ከአራቱ ወንጌላት አንደኛው ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ አዲስ ኪዳን ውስጥ ከሁሉ በፊት ይገኛል። በዕብራይስጥና በአርማይስጥ ቋንቋ ማቴዎስ ማለት ሀብተ አምላክ ወይም የአምላክ ስጦታ ማለት እንደሆነ ይነገራል ። በአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የስም ዝርዝር ውስጥ በሁለተኛውና በሦስተኛው ማለትም በማርቆስና በሉቃስ ወንጌል በተራ ቁጥር ሰባተኛ ሲሆን ስሙም ማቴዎስ በመባል ተመዝግቦአል (ማር.፫:፲፮-፲፱ ፡ ሉቃ.፮:፲፬-፲፮) ።

ራሱ በጻፈው ወንጌልና በሐዋርያት ሥራ ደግሞ በተራ ቁጥር ስምንተኛ ሆኖ ማቴዎስ በመባል ተመዝግቦአል (ማቴ.፲: ፪-፬ ፡ የሐ.ሥ.፩-፲፫) ሌዊ ለሐዋርያነት ከመመረጡ በፊት የተጠራበት ስሙ ሲሆን ማቴዎስ ደግሞ ለወንጌል አገልግሎት በሐዋርያነት ከተጠራ በኋላ የተጠራበት ስሙ ነው ።

የመጀመሪያ ሥራው

ቅዱስ ማቴዎስ ለሐዋርያነት ከመጠራቱ በፊት ሥራው በግዕዝ (ሊቀ መጽብሐን) ማለት ቀራጭ ነበረ ። በአዲስ ኪዳን የትምህርት አገላለጽ ቀራጮች እንደ አመንዝሮች ፣ ዓመፀኞቾ ፣ ይቆጠሩ ነበር (ሉቃ.፲፰፡፲፩-፲፪)። በዚህ አንጻር ማቴዎስ ቀራጭ እንደመሆኑ መጠን የዘመኑ የሃይማኖት ሰዎች ይጠሉት ነበር ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማቴዎስን በመቅረጫው ባታ አገኘውና "ተከተለኝ"በማለት ስለ ጠራው ሁሉን ትቶ ተከተለው (ማቴ.፱፣፱)። ቀራጩ ማቴዎስ ሐዋርያና ወንጌላዊ ሆነ ፣ መደቡ ከአረመኔዎችና ከአመፀኞች ጋር የነበረው ሌዊ ከአሥራ ሁለቱ ቅዱሳን ሐዋርያት ጋር ተቆጠረ ። ወንጌልን ጌታ ከአረገ ስምንተኛው ተፈጽሞ ዘጠነኛው ሲጀምር ቀላውዴዎስ ቄሣር በነገሠ በመጀመሪያው ዓመት በዕብራይስጥ ቋንቋ ጻፈ ። አሁን መጀመርያ የምናውቀው ቅጂ በግሪክኛ ቢሆንም፣ ጽሑፉ በዕብራይስጥ እንደ ተቀነባበረ ከጥንት ጀምሮ በልማድ እንዲሁም እስካሁን በዛሬ ሊቃውንት ታስቧል። ክርስቶስ "የመጣሁት ለበሽተኞች እንጂ ለደኅነኞች አይደለም" ያለበትም ማቴዎስ በመኖሪያው ቤቱ ግብዣ አድርጎ ክርስቶስን ጋብዞ ከቀራጮች ጋር አብሮ ሲበላ ፣ ፈሪሳውያን "ከኃጢያተኞች ጋር ትተባበራለህ" ብለው በመተቸታቸው ሆነ ።

ምልክቱ

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከአብርሃምና ከዳዊት ዘር መወለዱን ለማስረዳት ከአብርሃም እስከ ቅድስት ድንግል ማርያም ድረስ በሰፊው ስለጻፈ ከጥንት ጀምሮ ማቴዎስ በገጸ ሰብእ ተመስሎአል ። ከሦስቱ ወንጌላውያን ይልቅ በማቴዎስ ወንጌል ከክርስቶስ ወልደ እጓል እምሕያው ፣ የሰው ልጅ በመባል ብዙ ጊዜ ስለተጠራ ለማቴዎስ የገጸ ሰብእ ምልክት ከአሰጡት ምክኒያቶች አንዱ ነው ።

ምዕራፍ ፩

1፤የዳዊት፡ልጅ፡የአብርሃም፡ልጅ፡የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ትውልድ፡መጽሐፍ። 2፤አብርሃም፡ይሥሐቅን፡ወለደ፤ይሥሐቅም፡ያዕቆብን፡ወለደ፤ያዕቆብም፡ይሁዳንና፡ወንድሞቹን፡ወለደ፤ 3፤ይሁዳም፡ከትዕማር፡ፋሬስንና፡ዛራን፡ወለደ፤ፋሬስም፡ኤስሮምን፡ወለደ፤4፤ኤስሮምም፡አራምን፡ወለደ፤አራምም፡ዐሚናዳብን፡ወለደ፤ዐሚናዳብም፡ነአሶንን፡ወለደ፤ነአሶንም፡ ሰልሞንን፡ወለደ፤ 5፤ሰልሞንም፡ከራኬብ፡ቦኤዝን፡ወለደ፤ቦኤዝም፡ከሩት፡ኢዮቤድን፡ወለደ፤ኢዮቤድም፡እሴይን፡ወለደ፤ 6፤እሴይም፡ንጉሥ፡ዳዊትን፡ወለደ። 7፤ሰሎሞንም፡ሮብዓምን፡ወለደ፤ሮብዓምም፡አቢያን፡ወለደ፤አቢያም፡አሣፍን፡ወለደ፤ 8፤አሣፍም፡ኢዮሳፍጥን፡ወለደ፤ኢዮሳፍጥም፡ኢዮራምን፡ወለደ፤ኢዮራምም፡ዖዝያንን፡ወለደ፤ 9፤ዖዝያንም፡ኢዮአታምን፡ወለደ፤ኢዮአታምም፡አካዝን፡ወለደ፤ 10፤አካዝም፡ሕዝቅያስን፡ወለደ፤ሕዝቅያስም፡ምናሴን፡ወለደ፤ምናሴም፡አሞፅን፡ወለደ፤ 11፤አሞፅም፡ኢዮስያስን፡ወለደ፤ኢዮስያስም፡በባቢሎን፡ምርኮ፡ጊዜ፡ኢኮንያንንና፡ወንድሞቹን፡ወለደ። 12፤ከባቢሎንም፡ምርኮ፡በዃላ፡ኢኮንያን፡ሰላትያልን፡ወለደ፤ሰላትያልም፡ዘሩባቤልን፡ወለደ፤ 13፤ዘሩባቤልም፡አብዩድን፡ወለደ፤አብዩድም፡ኤልያቄምን፡ወለደ፤ኤልያቄምም፡ዐዛርን፡ወለደ፤ 14፤ዐዛርም፡ሳዶቅን፡ወለደ፤ሳዶቅም፡አኪምን፡ወለደ፤አኪምም፡ኤልዩድን፡ወለደ፤ 15፤ኤልዩድም፡አልዓዛርን፡ወለደ፤አልዓዛርም፡ማታንን፡ወለደ፤ማታንም፡ያዕቆብን፡ወለደ፤ 16፤ያዕቆብም፡ክርስቶስ፡የተባለውን፡ኢየሱስን፡የወለደች፡የማርያምን፡ዕጮኛ፡ዮሴፍን፡ወለደ። 17፤እንግዲህ፡ትውልድ፡ዅሉ፡ከአብርሃም፡እስከ፡ዳዊት፡ዐሥራ፡አራት፡ትውልድ፥ከዳዊትም፡እስከባቢሎን፡ ምርኮ፡ዐሥራ፡አራት፡ትውልድ፥ከባቢሎንም፡ምርኮ፡እስከ፡ክርስቶስ፡ዐሥራ፡አራት፡ትውልድ፡ነው። 18፤የኢየሱስ፡ክርስቶስም፡ልደት፡እንዲህ፡ነበረ።እናቱ፡ማርያም፡ለዮሴፍ፡በታጨች፡ጊዜ፥ሳይገናኙ፡ ከመንፈስ፡ቅዱስ፡ፀንሳ፡ተገኘች። 19፤ዕጮኛዋ፡ዮሴፍም፡ጻድቅ፡ኾኖ፡ሊገልጣት፡ስላልወደደ፥በስውር፡ሊተዋት፡ዐሰበ። 20፤ርሱ፡ግን፡ይህን፡ሲያስብ፥እንሆ፥የጌታ፡መልአክ፡በሕልም፡ታየው፥እንዲህም፡አለ፦የዳዊት፡ልጅ፡ዮሴፍ፡ሆይ፥ከርሷ፡የተፀነሰው፡ከመንፈስ፡ቅዱስ፡ነውና፥ዕጮኛኽን፡ማርያምን፡ለመውሰድ፡አትፍራ።

    • ግ.፥የሱስ፡(መድኅን)፥(ዕብ.፥የሆሹዐ)፤'ኢ'፡ከጽርእ፡'የውጣ-ι'፡የተወረሰ፡ትርፍ፡ነው።
    • ግ.፥መሲሕ፡(ዕብ.፥መሺያሕ)።'ክርስቶስ'፡የሚለው፡ቃል፡በጽርእ፡'ኅሪዖ-የተቀባ፥ምርጥ'፡፡ካለው፡የወጣ፡ነው፤
    • ከ'ኅረየ'፡የተገኘ፡ይመስላል።ትኽክለኛው፡የግእዝ፡አጠራሩ፡'መሲሕ'፡ቢኾንም፥ሐዲስ፡ኪዳን፡ከጽርእ፡ወደ፡ግእዝ፡ሲመለስ፥ብዙ፡የስም አጠራሮች፡ከጽርኡ፡በተቀዱበት፡አባባል፡እስከ፡ዘመናችን፡ደርሰዋል፤ወደ፡ፊት፡ቢስተካከሉ፡ይበጃል።

21፤ልጅም፡ትወልዳለች፤ርሱ፡ሕዝቡን፡ከኀጢአታቸው፡ያድናቸዋልና፥ስሙን፡ኢየሱስ፡ትለዋለኽ። 22፤በነቢይ፡ከጌታ፡ዘንድ፦ 23፤እንሆ፥ድንግል፡ትፀንሳለች፡ልጅም፡ትወልዳለች፥ስሙንም፡ዐማኑኤል፡ይሉታል፡የተባለው፡ይፈጸም፡ ዘንድ፡ይህ፡ዅሉ፡ኾኗል፥ትርጓሜውም፦እግዚአብሔር፡ከእኛ፡ጋራ፡የሚል፡ነው። 24፤ዮሴፍም፡ከእንቅልፉ፡ነቅቶ፡የጌታ፡መልአክ፡እንዳዘዘው፡አደረገ፤ዕጮኛውንም፡ወሰደ፤ 25፤የበኵር፡ልጇንም፡እስክትወልድ፡ድረስ፡አላወቃትም፤ስሙንም፡ኢየሱስ፡አለው።

ምዕራፍ ፪

1-2፤ኢየሱስም፡በይሁዳ፡ቤተ፡ልሔም፡በንጉሡ፡በሄሮድስ፡ዘመን፡በተወለደ፡ጊዜ፥እንሆ፥ሰብአ፡ ሰገል፦የተወለደው፡የአይሁድ፡ንጉሥ፡ወዴት፡ነው፧ኮከቡን፡በምሥራቅ፡አይተን፡ልንሰግድለት፡ መጥተናልና፥እያሉ፡ከምሥራቅ፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡መጡ። 3፤ንጉሡ፡ሄሮድስም፡ሰምቶ፡ደነገጠ፥ኢየሩሳሌምም፡ዅሉ፡ከርሱ፡ጋራ፤ 4፤የካህናትንም፡አለቃዎች፡የሕዝቡንም፡ጻፊዎች፡ዅሉ፡ሰብስቦ፡ክርስቶስ፡ወዴት፡እንዲወለድ፡ጠየቃቸው። 5-6፤እነርሱም፦አንቺ፡ቤተ፡ልሔም፥የይሁዳ፡ምድር፥ከይሁዳ፡ገዢዎች፡ከቶ፡አታንሺም፤ሕዝቤን፡እስራኤልን፡የሚጠብቅ፡መስፍን፡ከአንቺ፡ይወጣልና፥ተብሎ፡በነቢይ፡እንዲህ፡ተጽፏልና፥በይሁዳ፡ቤተ፡ ልሔም፡ነው፡አሉት። 7፤ከዚህ፡በዃላ፡ሄሮድስ፡ሰብአ፡ሰገልን፡በስውር፡ጠርቶ፡ኮከቡ፡የታየበትን፡ዘመን፡ከነርሱ፡በጥንቃቄ፡ተረዳ፥ 8፤ወደ፡ቤተ፡ልሔምም፡እነርሱን፡ሰዶ፟፦ኺዱ፥ስለ፡ሕፃኑ፡በጥንቃቄ፡መርምሩ፤ባገኛችኹትም፡ጊዜ፡እኔ፡ ደግሞ፡መጥቼ፡እንድሰግድለት፡ንገሩኝ፡አላቸው። 9፤እነርሱም፡ንጉሡን፡ሰምተው፡ኼዱ፤እንሆም፥በምሥራቅ፡ያዩት፡ኮከብ፡ሕፃኑ፡ባለበት፡ላይ፡መጥቶ፡ እስኪቆም፡ድረስ፡ይመራቸው፡ነበር። 10፤ኮከቡንም፡ባዩ፡ጊዜ፡በታላቅ፡ደስታ፡እጅግ፡ደስ፡አላቸው። 11፤ወደ፡ቤትም፡ገብተው፡ሕፃኑን፡ከእናቱ፡ከማርያም፡ጋራ፡አዩት፥ወድቀውም ሰገዱለት፥ሣጥኖቻቸውንም፡ ከፍተው፡እጅ፡መንሻ፡ወርቅና፡ዕጣን፡ከርቤም፡አቀረቡለት። 12፤ወደ፡ሄሮድስም፡እንዳይመለሱ፡በሕልም፡ተረድተው፡በሌላ፡መንገድ፡ወደ፡አገራቸው፡ኼዱ። 13፤እነርሱም፡ከኼዱ፡በዃላ፥እንሆ፥የጌታ፡መልአክ፡በሕልም፡ለዮሴፍ፡ታይቶ፦ሄሮድስ፡ሕፃኑን፡ ሊገድለው፡ይፈልገዋልና፥ተነሣ፥ሕፃኑንና፡እናቱንም፡ይዘኽ፡ወደ፡ግብጽ፡ሽሽ፥እስክነግርኽም፡ድረስ፡በዚያ፡ ተቀመጥ፡አለው። 14-15፤ርሱም፡ተነሥቶ፡ሕፃኑንና፡እናቱን፡በሌሊት፡ያዘና፡ከጌታ፡ዘንድ፡በነቢይ፦ልጄን፡ከግብጽ፡ጠራኹት፡የተባለው፡እንዲፈጸም፥ወደ፡ግብጽ፡ኼደ፥ሄሮድስም፡እስኪሞት፡ድረስ፡በዚያ፡ኖረ። 16፤ከዚህ፡በዃላ፡ሄሮድስ፡ሰብአ፡ሰገል፡እንደ፡ተሣለቁበት፡ባየ፡ጊዜ፡እጅግ፡ተቈጣና፡ልኮ፡ከሰብአ፡ሰገል፡ እንደ፡ተረዳው፡ዘመን፡በቤተ፡ልሔምና፡በአውራጃዋ፡የነበሩትን፥ኹለት፡ዓመት፡የኾናቸውን፡ከዚያም፡ የሚያንሱትን፡ሕፃናት፡ዅሉ፡አስገደለ። 17-18፤ያን፡ጊዜ፡በነቢዩ፡በኤርምያስ፥ድምፅ፡በራማ፡ተሰማ፥ልቅሶና፡ብዙ፡ዋይታ፤ራሔል፡ስለ፡ልጆቿ፡ አለቀሰች፥መጽናናትም፡አልወደደችም፥የሉምና፡የተባለው፡ተፈጸመ። 19፤ሄሮድስም፡ከሞተ፡በዃላ፥እንሆ፥የጌታ፡መልአክ፡በግብጽ፡ለዮሴፍ፡በሕልም፡ታይቶ፦20፤የሕፃኑን፡ነፍስ፡የፈለጉት፡ሞተዋልና፥ተነሣ፥ሕፃኑን፡እናቱንም፡ይዘኽ፡ወደእስራኤል፡አገር፡ኺድ፡አለ። 21፤ርሱም፡ተነሥቶ፡ሕፃኑንና፡እናቱን፡ያዘና፡ወደእስራኤል፡አገር፡ገባ። 22፤በአባቱም፡በሄሮድስ፡ፈንታ፡አርኬላዎስ፡በይሁዳ፡እንደ፡ነገሠ፡በሰማ፡ጊዜ፥ወደዚያ፡መኼድን፡ ፈራ፤በሕልምም፡ተረድቶ፡ወደገሊላ፡አገር፡ኼደ፤ 23፤በነቢያት፡ናዝራዊ፡ይባላል፡የተባለው፡ይፈጸም፡ዘንድ፥ናዝሬት፡ወደምትባል፡ከተማ፡መጥቶ፡ኖረ።

ምዕራፍ ፫

1-2፤በዚያም፡ወራት፡መጥምቁ፡ዮሐንስ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡ቀርባለችና፡ንስሓ፡ግቡ፡ብሎ፡በይሁዳ፡ ምድረ፡በዳ፡እየሰበከ፡መጣ። 3፤በነቢዩ፡በኢሳይያስ፦የጌታን፡መንገድ፡አዘጋጁ፡ጥርጊያውንም፡አቅኑ፡እያለ፡በምድረ፡በዳ፡የሚጮኽ፡ ሰው፡ድምፅ፡የተባለለት፡ይህ፡ነውና። 4፤ራሱም፡ዮሐንስ፡የግመል፡ጠጕር፡ልብስ፡ነበረው፥በወገቡም፡ጠፍር፡ይታጠቅ፡ነበር፤ምግቡም፡አንበጣና፡ የበረሓ፡ማር፡ነበረ። 5፤ያን፡ጊዜ፡ኢየሩሳሌም፡ይሁዳም፡ዅሉ፡በዮርዳኖስም፡ዙሪያ፡ያለ፡አገር፡ዅሉ፡ወደ፡ርሱ፡ይወጡ፡ነበር፤ 6፤ኀጢአታቸውንም፡እየተናዘዙ፡በዮርዳኖስ፡ወንዝ፡ከርሱ፡ይጠመቁ፡ነበር። 7፤ዳሩ፡ግን፡ከፈሪሳውያንና፡ከሰዱቃውያን፡ብዙዎች፡ወደ፡ጥምቀቱ፡ሲመጡ፡ባየ፡ጊዜ፥እንዲህ፡ አላቸው፦እናንተ፡የእፍኝት፡ልጆች፥ከሚመጣው፡ቍጣ፡እንድትሸሹ፡ማን፡አመለከታችኹ፧ 8፤እንግዲህ፡ለንስሓ፡የሚገ፟ባ፟፡ፍሬ፡አድርጉ፤ 9፤በልባችኹም፦አብርሃም፡አባት፡አለን፡እንደምትሉ፡አይምሰላችኹ፤እላችዃለኹና፦ከነዚህ፡ድንጋዮች፡ ለአብርሃም፡ልጆች፡ሊያስነሣለት፡እግዚአብሔር፡ይችላል። 10፤አኹንስ፡ምሣር፡በዛፎች፡ሥር፡ተቀምጧል፤እንግዲህ፡መልካም፡ፍሬ፡የማያደርግ፡ዛፍ፡ዅሉ፡ይቈረጣል፡ ወደ፡እሳትም፡ይጣላል። 11፤እኔስ፡ለንስሓ፡በውሃ፡አጠምቃችዃለኹ፤ጫማውን፡እሸከም፡ዘንድ፡የማይገ፟ባ፟ኝ፡ከእኔ፡በዃላ፡ የሚመጣው፡ግን፡ከእኔ፡ይልቅ፡ይበረታል፤ርሱ፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡በእሳትም፡ያጠምቃችዃል፤ 12፤መንሹም፡በእጁ፡ነው፥ዐውድማውንም፡ፈጽሞ፡ያጠራል፥ስንዴውንም፡በጐተራው፡ይከታል፥ገለባውን፡ ግን፡በማይጠፋ፡እሳት፡ያቃጥለዋል። 13፤ያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡በዮሐንስ፡ሊጠመቅ፡ከገሊላ፡ወደ፡ዮርዳኖስ፡መጣ። 14፤ዮሐንስ፡ግን፦እኔ፡ባንተ፡ልጠመቅ፡ያስፈልገኛል፡አንተም፡ወደ፡እኔ፡ትመጣለኽን፧ብሎ፡ይከለክለው፡ ነበር። 15፤ኢየሱስም፡መልሶ፦አኹንስ፡ፍቀድልኝ፤እንዲህ፡ጽድቅን፡ዅሉ፡መፈጸም፡ይገ፟ባ፟ናልና፥አለው።ያን፡ ጊዜ፡ፈቀደለት። 16፤ኢየሱስም፡ከተጠመቀ፡በዃላ፡ወዲያው፡ከውሃ፡ወጣ፤እንሆም፥ሰማያት፡ተከፈቱ፡የእግዚአብሔርም፡ መንፈስ፡እንደ፡ርግብ፡ሲወርድ፡በርሱ፡ላይም፡ሲመጣ፡አየ፤ 17፤እንሆም፥ድምፅ፡ከሰማያት፡መጥቶ፦በርሱ፡ደስ፡የሚለኝ፡የምወደ፟ው፡ልጄ፡ይህ፡ነው፡አለ።

ምዕራፍ ፬

1፤ከዚያ፡ወዲያ፡ኢየሱስ፡ከዲያብሎስ፡ይፈተን፡ዘንድ፡መንፈስ፡ወደ፡ምድረ፡በዳ፡ወሰደው፥ 2፤አርባ፡ቀንና፡አርባ፡ሌሊትም፡ከጦመ፡በዃላ፡ተራበ። 3፤ፈታኝም፡ቀርቦ፦የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ከኾንኽ፥እነዚህ፡ድንጋዮች፡እንጀራ፡እንዲኾኑ፡በል፡አለው። 4፤ርሱም፡መልሶ፦ሰው፡ከእግዚአብሔር፡አፍ፡በሚወጣ፡ቃል፡ዅሉ፡እንጂ፡በእንጀራ፡ብቻ፡አይኖርም፡ ተብሎ፡ተጽፏል፡አለው። 5፤ከዚህ፡በዃላ፡ዲያብሎስ፡ወደ፡ቅድስት፡ከተማ፡ወሰደውና፡ርሱን፡በመቅደስ፡ጫፍ፡ላይ፡አቁሞ፦ 6፤መላእክቱን፡ስለ፡አንተ፡ያዝልኻል፡እግርኽንም፡በድንጋይ፡ከቶ፡እንዳትሰናከል፡በእጃቸው፡ያነሡኻል፡ ተብሎ፡ተጽፏልና፥የእግዚአብሔር፡ልጅስ፡ከኾንኽ፥ወደ፡ታች፡ራስኽን፡ወርውር፡አለው። 7፤ኢየሱስም፦ጌታን፡አምላክኽን፡አትፈታተነው፡ተብሎ፡ደግሞ፡ተጽፏል፡አለው። 8፤ደግሞ፡ዲያብሎስ፡እጅግ፡ረዥም፡ወደ፡ኾነ፡ተራራ፡ወሰደው፥የዓለምንም፡መንግሥታት፡ዅሉ፡ ክብራቸውንም፡አሳይቶ፦9፤ወድቀኽ፡ብትሰግድልኝ፡ይህን፡ዅሉ፡እሰጥኻለኹ፡አለው። 10፤ያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፦ኺድ፥አንተ፡ሰይጣን፡ለጌታኽ፡ለአምላክኽ፡ስገድ፡ርሱንም፡ብቻ፡አምልክ፡ተብሎ፡ ተጽፏልና፥አለው። 11፤ያን፡ጊዜ፡ዲያብሎስ፡ተወው፥እንሆም፥መላእክት፡ቀርበው፡ያገለግሉት፡ነበር። 12፤ኢየሱስም፡ዮሐንስ፡ዐልፎ፡እንደ፡ተሰጠ፡በሰማ፡ጊዜ፡ወደ፡ገሊላ፡ፈቀቅ፡ብሎ፡ኼደ። 13፤ናዝሬትንም፡ትቶ፡በዛብሎንና፡በንፍታሌም፡አገር፡በባሕር፡አጠገብ፡ወዳለችው፡ወደ፡ቅፍርናሖም፡መጥቶ፡ኖረ። 14-16፤በነቢዩም፡በኢሳይያስ፦የዛብሎን፡ምድርና፡የንፍታሌም፡ምድር፥የባሕር፡መንገድ፥በዮርዳኖስ፡ ማዶ፥የአሕዛብ፡ገሊላ፤በጨለማ፡የተቀመጠው፡ሕዝብ፡ታላቅ፡ብርሃን፡አየ፥በሞት፡አገርና፡ጥላ፡ ለተቀመጡትም፡ብርሃን፡ወጣላቸው፡ 17፤የተባለው፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ይህ፡ኾነ።ከዚያ፡ዘመን፡ዠምሮ፡ኢየሱስ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡ቀርባለችና፡ ንስሓ፡ግቡ፡እያለ፡ይሰብክ፡ዠመር። 18፤በገሊላ፡ባሕር፡አጠገብ፡ሲመላለስም፡ኹለት፡ወንድማማች፡ጴጥሮስ፡የሚሉትን፡ስምዖንን፡ወንድሙንም፡ እንድርያስን፡መረባቸውን፡ወደ፡ባሕር፡ሲጥሉ፡አየ፥ዓሣ፡አጥማጆች፡ነበሩና። 19፤ርሱም፦በዃላዬ፡ኑና፡ሰዎችን፡አጥማጆች፡እንድትኾኑ፡አደርጋችዃለኹ፡አላቸው። 20፤ወዲያውም፡መረባቸውን፡ትተው፡ተከተሉት። 21፤ከዚያም፡እልፍ፡ብሎ፡ሌላዎችን፡ኹለት፡ወንድማማች፡የዘብዴዎስን፡ልጅ፡ያዕቆብን፡ወንድሙንም፡ ዮሐንስን፡ከአባታቸው፡ከዘብዴዎስ፡ጋራ፡በታንኳ፡መረባቸውን፡ሲያበጁ፡አየ፤ጠራቸውም። 22፤እነርሱም፡ወዲያው፡ታንኳዪቱንና፡አባታቸውን፡ትተው፡ተከተሉት። 23፤ኢየሱስም፡በምኵራቦቻቸው፡እያስተማረ፡የመንግሥትንም፡ወንጌል፡እየሰበከ፡በሕዝብም፡ያለውን፡ደዌና፡ ሕማም፡ዅሉ፡እየፈወሰ፡በገሊላ፡ዅሉ፡ይዞር፡ነበር። 24፤ዝናውም፡ወደ፡ሶርያ፡ዅሉ፡ወጣ፤በልዩ፡ልዩ፡ደዌና፡ሥቃይም፡ተይዘው፡የታመሙትን፡ዅሉ፡ አጋንንትም፡ያደሩባቸውን፡በጨረቃም፡የሚነሣባቸውን፡ሽባዎችንም፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ፥ፈወሳቸውም። 25፤ከገሊላም፡ከዐሥሩ፡ከተማም፡ከኢየሩሳሌምም፡ከይሁዳም፡ከዮርዳኖስም፡ማዶ፡ብዙ፡ሕዝብ፡ተከተሉት።

ምዕራፍ ፭

1፤ሕዝቡንም፡አይቶ፡ወደ፡ተራራ፡ወጣ፤በተቀመጠም፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ወደ፡ርሱ፡ቀረቡ፤ 2፤አፉንም፡ከፍቶ፡አስተማራቸው፡እንዲህም፡አለ። 3፤በመንፈስ፡ድኻዎች፡የኾኑ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መንግሥተ፡ሰማያት፡የእነርሱ፡ናትና። 4፤የሚያዝኑ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መጽናናትን፡ያገኛሉና። 5፤የዋሆች፡ብፁዓን፡ናቸው፥ምድርን፡ይወርሳሉና።6፤ጽድቅን፡የሚራቡና፡የሚጠሙ፡ብፁዓን፡ናቸው፥ይጠግባሉና። 7፤የሚምሩ፡ብፁዓን፡ናቸው፥ይማራሉና። 8፤ልበ፡ንጹሖች፡ብፁዓን፡ናቸው፥እግዚአብሔርን፡ያዩታልና። 9፤የሚያስተራርቁ፡ብፁዓን፡ናቸው፥የእግዚአብሔር፡ልጆች፡ይባላሉና። 10፤ስለ፡ጽድቅ፡የሚሰደዱ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መንግሥተ፡ሰማያት፡የእነርሱ፡ናትና። 11፤ሲነቅፏችኹና፡ሲያሳድዷችኹ፡በእኔም፡ምክንያት፡ክፉውን፡ዅሉ፡በውሸት፡ሲናገሩባችኹ፡ብፁዓን፡ናችኹ። 12፤ዋጋችኹ፡በሰማያት፡ታላቅ፡ነውና፥ደስ፡ይበላችኹ፥ሐሴትም፡አድርጉ፤ከእናንተ፡በፊት፡የነበሩትን፡ ነቢያትን፡እንዲሁ፡አሳደ፟ዋቸዋልና። 13፤እናንተ፡የምድር፡ጨው፡ናችኹ፤ጨው፡ዐልጫ፡ቢኾን፡ግን፡በምን፡ይጣፍጣል፧ወደ፡ውጭ፡ተጥሎ፡ በሰው፡ከመረገጥ፡በቀር፡ወደ፡ፊት፡ለምንም፡አይጠቅምም። 14፤እናንተ፡የዓለም፡ብርሃን፡ናችኹ።በተራራ፡ላይ፡ያለች፡ከተማ፡ልትሰወር፡አይቻላትም። 15፤መብራትንም፡አብርተው፡ከእንቅብ፡በታች፡አይደለም፡እንጂ፡በመቅረዙ፡ላይ፡ያኖሩታል፡በቤት፡ላሉት፡ ዅሉም፡ያበራል። 16፤መልካሙን፡ሥራችኹን፡አይተው፡በሰማያት፡ያለውን፡አባታችኹን፡እንዲያከብሩ፡ብርሃናችኹ፡እንዲሁ፡ በሰው፡ፊት፡ይብራ። 17፤እኔ፡ሕግንና፡ነቢያትን፡ለመሻር፡የመጣኹ፡አይምሰላችኹ፤ልፈጽም፡እንጂ፡ለመሻር፡አልመጣኹም። 18፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ሰማይና፡ምድር፡እስኪያልፍ፡ድረስ፥ከሕግ፡አንዲት፡የውጣ፡ወይም፡አንዲት፡ ነጥብ፡ከቶ፡አታልፍም፥ዅሉ፡እስኪፈጸም፡ድረስ። 19፤እንግዲህ፡ከነዚህ፡ከዅሉ፡ካነሱት፡ትእዛዛት፡አንዲቱን፡የሚሽር፡ለሰውም፡እንዲሁ፡የሚያስተምር፡ማንም፡ሰው፡በመንግሥተ፡ሰማያት፡ከዅሉ፡ታናሽ፡ይባላል፤የሚያደርግ፡ግን፡የሚያስተምርም፡ማንም፡ቢኾን፡ርሱ፡ በመንግሥተ፡ሰማያት፡ታላቅ፡ይባላል። 20፤እላችዃለኹና፦ጽድቃችኹ፡ከጻፊዎችና፡ከፈሪሳውያን፡ጽድቅ፡ካልበለጠ፥ወደ፡መንግሥተ፡ሰማያት፡ከቶ፡ አትገቡም። 21፤ለቀደሙት፦አትግደል፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችዃል፤የገደለም፡ዅሉ፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል። 22፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥በወንድሙ፡ላይ፡የሚቈጣ፡ዅሉ፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል፤ወንድሙንም፡ጨርቃም፡ የሚለው፡ዅሉ፡የሸንጎ፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል፤ደንቈሮ፡የሚለውም፡ዅሉ፡የገሃነመ፡እሳት፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል። 23፤እንግዲህ፡መባኽን፡በመሠዊያው፡ላይ፡ብታቀርብ፥በዚያም፡ወንድምኽ፡አንዳች፡ባንተ፡ላይ፡እንዳለው፡ ብታስብ፥ 24፤በዚያ፡በመሠዊያው፡ፊት፡መባኽን፡ትተኽ፡ኺድ፥አስቀድመኽም፡ከወንድምኽ፡ጋራ፡ታረቅ፥በዃላም፡ መጥተኽ፡መባኽን፡አቅርብ። 25፤ዐብረኸው፡በመንገድ፡ሳለኽ፡ከባላጋራኽ፡ጋራ፡ፈጥነኽ፡ተስማማ፤ባላጋራ፡ለዳኛ፡እንዳይሰጥኽ፡ዳኛም፡ ለሎሌው፥ወደ፡ወህኒም፡ትጣላለኽ፤ 26፤እውነት፡እልኻለኹ፥የመጨረሻዋን፡ሳንቲም፡እስክትከፍል፡ድረስ፡ከቶ፡ከዚያ፡አትወጣም። 27፤አታመንዝር፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችዃል። 28፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥ወደ፡ሴት፡ያየ፡ዅሉ፡የተመኛትም፡ያን፡ጊዜ፡በልቡ፡ከርሷ፡ጋራ፡ አመንዝሯል። 29፤ቀኝ፡ዐይንኽም፡ብታሰናክልኽ፡አውጥተኽ፡ከአንተ፡ጣላት፤ሙሉ፡ሰውነትኽ፡በገሃነም፡ከሚጣል፡ይልቅ፡ ከአካላትኽ፡አንድ፡ቢጠፋ፡ይሻልኻልና። 30፤ቀኝ፡እጅኽም፡ብታሰናክልኽ፡ቈርጠኽ፡ከአንተ፡ጣላት፤ሙሉ፡ሰውነትኽ፡በገሃነም፡ከሚጣል፡ይልቅ፡ ከአካላትኽ፡አንድ፡ቢጠፋ፡ይሻላልና። 31፤ሚስቱን፡የሚፈታት፡ዅሉ፡የፍቿን፡ጽሕፈት፡ይስጣት፡ተባለ። 32፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥ያለዝሙት፡ምክንያት፡ሚስቱን፡የሚፈታ፡ዅሉ፡አመንዝራ፡ ያደርጋታል፥የተፈታችውንም፡የሚያገባ፡ዅሉ፡ያመነዝራል። 33፤ደግሞ፡ለቀደሙት፦በውሸት፡አትማል፥ነገር፡ግን፥መሐላዎችኽን፡ለጌታ፡ስጥ፡አንደ፡ተባለ፡ ሰምታችዃል። 34፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፦ከቶ፡አትማሉ፤በሰማይ፡አይኾንም፡የእግዚአብሔር፡ዙፋን፡ነውና፤ 35፤በምድርም፡አይኾንም፡የእግሩ፡መረገጫ፡ናትና፤በኢየሩሳሌምም፡አይኾንም፡የታላቁ፡ንጉሥ፡ከተማ፡ ናትና፤ 36፤በራስኽም፡አትማል፥አንዲቱን፡ጠጕር፡ነጭ፡ወይም፡ጥቍር፡ልታደርግ፡አትችልምና። 37፤ነገር፡ግን፥ቃላችኹ፡አዎን፡አዎን፡ወይም፡አይደለም፡አይደለም፡ይኹን፤ከነዚህም፡የወጣ፡ከክፉው፡ ነው። 38፤ዐይን፡ስለ፡ዐይን፡ጥርስም፡ስለ፡ጥርስ፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችዃል። 39፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥ክፉውን፡አትቃወሙ፤ዳሩ፡ግን፡ቀኝ፡ጕንጭኽን፡በጥፊ፡ለሚመታኽ፡ዅሉ፡ ኹለተኛውን፡ደግሞ፡አዙርለት፤ 40፤እንዲከስኽም፡እጀ፡ጠባብኽንም፡እንዲወስድ፡ለሚወድ፡መጐናጸፊያኽን፡ደግሞ፡ተውለት፤ 41፤ማንም፡ሰው፡አንድ፡ምዕራፍ፡ትኼድ፡ዘንድ፡ቢያስገድድኽ፡ኹለተኛውን፡ከርሱ፡ጋራ፡ኺድ። 42፤ለሚለምንኽ፡ስጥ፥ከአንተም፡ይበደር፡ዘንድ፡ከሚወደ፟ው፡ፈቀቅ፡አትበል። 43፤ባልንጀራኽን፡ውደድ፡ጠላትኽንም፡ጥላ፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችዃል። 44-45፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥በሰማያት፡ላለ፡አባታችኹ፡ልጆች፡ትኾኑ፡ዘንድ፡ጠላቶቻችኹን፡ ውደዱ፥የሚረግሟችኹንም፡መርቁ፥ለሚጠሏችኹም፡መልካም፡አድርጉ፥ስለሚያሳድዷችኹም፡ጸልዩ፤ርሱ፡ በክፉዎችና፡በበጎዎች፡ላይ፡ፀሓይን፡ያወጣልና፥በጻድቃንና፡በኀጢአተኛዎችም፡ላይ፡ዝናቡን፡ያዘንባልና። 46፤የሚወዷ፟ችኹን፡ብትወዱ፡ምን፡ዋጋ፡አላችኹ፧ቀራጮችስ፡ያንኑ፡ያደርጉ፡የለምን፧ 47፤ወንድሞቻችኹንም፡ብቻ፡እጅ፡ብትነሡ፡ምን፡ብልጫ፡ታደርጋላችኹ፧አሕዛብስ፡ያንኑ፡ያደርጉ፡የለምን፧ 48፤እንግዲህ፡የሰማዩ፡አባታችኹ፡ፍጹም፡እንደ፡ኾነ፡እናንተ፡ፍጹማን፡ኹኑ።

ምዕራፍ ፮

1፤ለሰዎች፡ትታዩ፡ዘንድ፡ምጽዋታችኹን፡በፊታቸው፡እንዳታደርጉ፡ተጠንቀቁ፤ያለዚያ፡በሰማያት፡ባለው፡ አባታችኹ፡ዘንድ፡ዋጋ፡የላችኹም። 2፤እንግዲህ፡ምጽዋት፡ስታደርግ፥ግብዞች፡በሰው፡ዘንድ፡ሊከበሩ፡በምኵራብ፡በመንገድም፡እንደሚያደርጉ፡ በፊትኽ፡መለከት፡አታስነፋ፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ዋጋቸውን፡ተቀብለዋል። 3-4፤አንተ፡ግን፡ምጽዋት፡ስታደርግ፡ምጽዋትኽ፡በስውር፡እንዲኾን፡ቀኝኽ፡የምትሠራውን፡ግራኽ፡ አትወቅ፤በስውር፡የሚያይ፡አባትኽም፡በግልጥ፡ይከፍልኻል። 5፤ስትጸልዩም፡እንደ፡ግብዞች፡አትኹኑ፤ለሰው፡ይታዩ፡ዘንድ፡በምኵራብና፡በመንገድ፡ማእዘን፡ቆመው፡ መጸለይን፡ይወዳሉና፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ዋጋቸውን፡ተቀብለዋል። 6፤አንተ፡ግን፡ስትጸልይ፥ወደ፡ዕልፍኝኽ፡ግባ፥መዝጊያኽንም፡ዘግተኽ፡በስውር፡ላለው፡አባትኽ፡ ጸልይ፤በስውር፡የሚያይ፡አባትኽም፡በግልጥ፡ይከፍልኻል። 7፤አሕዛብም፡በመናገራቸው፡ብዛት፡እንዲሰሙ፡ይመስላቸዋልና፥ስትጸልዩ፡እንደ፡እነርሱ፡በከንቱ፡ አትድገሙ። 8፤ስለዚህ፥አትምሰሏቸው፤ሳትለምኑት፡አባታችኹ፡የሚያስፈልጋችኹን፡ያውቃልና። 9፤እንግዲህ፡እናንተስ፡እንዲህ፡ጸልዩ፦በሰማያት፡የምትኖር፡አባታችን፡ሆይ፥ 10፤ስምኽ፡ይቀደስ፤መንግሥትኽ፡ትምጣ፤ፈቃድኽ፡በሰማይ፡እንደ፡ኾነች፡እንዲሁ፡በምድር፡ትኹን፤ 11፤የዕለት፡እንጀራችንን፡ዛሬ፡ስጠን፤ 12፤እኛም፡ደግሞ፡የበደሉንን፡ይቅር፡እንደምንል፡በደላችንን፡ይቅር፡በለን፤ 13፤ከክፉም፡አድነን፡እንጂ፡ወደ፡ፈተና፡አታግባን፤መንግሥት፡ያንተ፡ናትና፥ኀይልም፡ክብርም፡ ለዘለዓለሙ፤አሜን። 14፤ለሰዎች፡ኀጢአታቸውን፡ይቅር፡ብትሉ፥የሰማዩ፡አባታችኹ፡እናንተን፡ደግሞ፡ይቅር፡ይላችዃልና፤ 15፤ለሰዎች፡ግን፡ኀጢአታቸውን፡ይቅር፡ባትሉ፥አባታችኹም፡ኀጢአታችኹን፡ይቅር፡አይላችኹም። 16፤ስትጦሙም፥እንደ፡ግብዞች፡አትጠውልጉ፤ለሰዎች፡እንደ፡ጦመኛ፡ሊታዩ፡ፊታቸውን፡ ያጠፋሉና፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ዋጋቸውን፡ተቀብለዋል። 17-18፤አንተ፡ግን፡ስትጦም፥በስውር፡ላለው፡አባትኽ፡እንጂ፡እንደ፡ጦመኛ፡ለሰዎች፡እንዳትታይ፡ራስኽን፡ ተቀባ፡ፊትኽንም፡ታጠብ፤በስውር፡የሚያይ፡አባትኽም፡በግልጥ፡ይከፍልኻል። 19፤ብልና፡ዝገት፡በሚያጠፉት፡ሌባዎችም፡ቈፍረው፡በሚሠርቁት፡ዘንድ፡ለእናንተ፡በምድር፡ላይ፡መዝገብ፡ አትሰብስቡ፤ 20፤ነገር፡ግን፥ብልም፡ዝገትም፡በማያጠፉት፡ሌባዎችም፡ቈፍረው፡በማይሠርቁት፡ዘንድ፡ለእናንተ፡በሰማይ፡ መዝገብ፡ሰብስቡ፤ 21፤መዝገብኽ፡ባለበት፡ልብኽ፡ደግሞ፡በዚያ፡ይኾናልና። 22፤የሰውነት፡መብራት፡ዐይን፡ናት።ዐይንኽ፡እንግዲህ፡ጤናማ፡ብትኾን፥ሰውነትኽ፡ዅሉ፡ብሩህ፡ይኾናል፤ 23፤ዐይንኽ፡ግን፡ታማሚ፡ብትኾን፥ሰውነትኽ፡ዅሉ፡የጨለመ፡ይኾናል።እንግዲህ፡ባንተ፡ያለው፡ብርሃን፡ ጨለማ፡ከኾነ፥ጨለማውስ፡እንዴት፡ይበረታ! 24፤ለኹለት፡ጌታዎች፡መገዛት፡የሚቻለው፡ማንም፡የለም፤ወይም፡አንዱን፡ይጠላል፡ኹለተኛውንም፡ ይወዳል፤ወይም፡ወደ፡አንዱ፡ይጠጋል፡ኹለተኛውንም፡ይንቃል፤ለእግዚአብሔርና፡ለገንዘብ፡መገዛት፡ አትችሉም። 25፤ስለዚህ፥እላችዃለኹ፥ስለ፡ነፍሳችኹ፡በምትበሉትና፡በምትጠጡት፥ወይም፡ስለ፡ሰውነታችኹ፡ በምትለብሱት፡አትጨነቁ፤ነፍስ፡ከመብል፣ሰውነትም፡ከልብስ፡አይበልጥምን፧ 26፤ወደ፡ሰማይ፡ወፎች፡ተመልከቱ፤አይዘሩም፡አያጭዱምም፡በጐተራም፡አይከቱም፥የሰማዩ፡አባታችኹም፡ ይመግባቸዋል፤እናንተ፡ከነርሱ፡እጅግ፡አትበልጡምን፧ 27፤ከእናንተ፡ተጨንቆ፡በቁመቱ፡ላይ፡አንድ፡ክንድ፡መጨመር፡የሚችል፡ማን፡ነው፧ 28፤ስለ፡ልብስስ፡ስለ፡ምን፡ትጨነቃላችኹ፧የሜዳ፡አበባዎች፡እንዴት፡እንዲያድጉ፡ልብ፡አድርጋችኹ፡ ተመልከቱ፤ 29፤አይደክሙም፡አይፈትሉምም፤ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥ሰሎሞንስ፡እንኳ፡በክብሩ፡ዅሉ፡ከነዚህ፡እንደ፡ አንዱ፡አልለበሰም። 30፤እግዚአብሔር፡ግን፡ዛሬ፡ያለውን፡ነገም፡ወደ፡እቶን፡የሚጣለውን፡የሜዳን፡ሣር፡እንዲህ፡የሚያለብሰው፡ ከኾነ፥እናንተ፡እምነት፡የጎደላችኹ፥እናንተንማ፡ይልቁን፡እንዴት፧ 31፤እንግዲህ፦ምን፡እንበላለን፧ምንስ፡እንጠጣለን፧ምንስ፡እንለብሳለን፧ብላችኹ፡አትጨነቁ፤ 32፤ይህንስ፡ዅሉ፡አሕዛብ፡ይፈልጋሉ፤ይህ፡ዅሉ፡እንዲያስፈልጋችኹ፡የሰማዩ፡አባታችኹ፡ያውቃልና። 33፤ነገር፡ግን፥አስቀድማችኹ፡የእግዚአብሔርን፡መንግሥት፡ጽድቁንም፡ፈልጉ፥ይህም፡ዅሉ፡ ይጨመርላችዃል። 34፤ነገ፡ለራሱ፡ይጨነቃልና፥ለነገ፡አትጨነቁ፤ለቀኑ፡ክፋቱ፡ይበቃዋል።

ምዕራፍ ፯

1-2፤እንዳይፈረድባችኹ፡አትፍረዱ፤በምትፈርዱበት፡ፍርድ፡ይፈረድባችዃልና፥በምትሰፍሩበትም፡መስፈሪያ፡ ይሰፈርባችዃል። 3፤በወንድምኽም፡ዐይን፡ያለውን፡ጕድፍ፡ስለ፡ምን፡ታያለኽ፥በዐይንኽ፡ግን፡ያለውን፡ምሰሶ፡ስለ፡ምን፡ አትመለከትም፧ 4፤ወይም፡ወንድምኽን፦ከዐይንኽ፡ጕድፍ፡ላውጣ፡ፍቀድልኝ፡እንዴትስ፡ትለዋለኽ፧እንሆም፥በዐይንኽ፡ ምሰሶ፡አለ። 5፤አንተ፡ግብዝ፥አስቀድመኽ፡ከዐይንኽ፡ምሰሶውን፡አውጣ፥ከዚያም፡በዃላ፡ከወንድምኽ፡ዐይን፡ጕድፉን፡ ታወጣ፡ዘንድ፡አጥርተኽ፡ታያለኽ። 6፤በእግራቸው፡እንዳይረግጡት፡ተመልሰውም፡እንዳይነክሷችኹ፥የተቀደሰውን፡ለውሻዎች፡ አትስጡ፥ዕንቍዎቻችኹንም፡በዕሪያዎች፡ፊት፡አትጣሉ። 7፤ለምኑ፥ይሰጣችኹማል፤ፈልጉ፥ታገኙማላችኹ፤መዝጊያን፡አንኳኩ፥ይከፈትላችኹማል። 8፤የሚለምነው፡ዅሉ፡ይቀበላልና፥የሚፈልገውም፡ያገኛል፥መዝጊያንም፡ለሚያንኳኳ፡ይከፈትለታል። 9፤ወይስ፡ከእናንተ፥ልጁ፡እንጀራ፡ቢለምነው፥ድንጋይን፡የሚሰጠው፡ከእናንተ፡ማን፡ሰው፡ነው፧ 10፤ዓሣስ፡ቢለምነው፡እባብን፡ይሰጠዋልን፧ 11፤እንኪያስ፡እናንተ፡ክፉዎች፡ስትኾኑ፡ለልጆቻችኹ፡መልካም፡ስጦታ፡መስጠትን፡ካወቃችኹ፥በሰማያት፡ ያለው፡አባታችኹ፡ለሚለምኑት፡እንዴት፡አብልጦ፡መልካም፡ነገርን፡ይሰጣቸው፧ 12፤እንግዲህ፡ሰዎች፡ሊያደርጉላችኹ፡የምትወዱትን፡ዅሉ፡እናንተ፡ደግሞ፡እንዲሁ፡አድርጉላቸው፤ሕግም፡ ነቢያትም፡ይህ፡ነውና። 13፤በጠበበው፡ደጅ፡ግቡ፤ወደ፡ጥፋት፡የሚወስደው፡ደጅ፡ሰፊ፥መንገዱም፡ትልቅ፡ነውና፥ወደ፡ርሱም፡የሚገቡ፡ብዙዎች፡ናቸው፤ 14፤ወደ፡ሕይወት፡የሚወስደው፡ደጅ፡የጠበበ፥መንገዱም፡የቀጠነ፡ነውና፥የሚያገኙትም፡ጥቂቶች፡ናቸው። 15፤የበግ፡ለምድ፡ለብሰው፡ከሚመጡባችኹ፡በውስጣቸው፡ግን፡ነጣቂዎች፡ተኵላዎች፡ከኾኑ፡ከሐሰተኛዎች፡ ነቢያት፡ተጠንቀቁ። 16፤ከፍሬያቸው፡ታውቋቸዋላችኹ።ከሾኽ፡ወይን፡ከኵርንችትስ፡በለስ፡ይለቀማልን፧ 17፤እንዲሁ፡መልካም፡ዛፍ፡ዅሉ፡መልካም፡ፍሬ፡ያደርጋል፥ክፉም፡ዛፍ፡ክፉ፡ፍሬ፡ያደርጋል። 18፤መልካም፡ዛፍ፡ክፉ፡ፍሬ፡ማፍራት፥ወይም፡ክፉ፡ዛፍ፡መልካም፡ፍሬ፡ማፍራት፡አይቻለውም። 19፤መልካም፡ፍሬ፡የማያደርግ፡ዛፍ፡ዅሉ፡ይቈረጣል፡ወደ፡እሳትም፡ይጣላል። 20፤ስለዚህም፡ከፍሬያቸው፡ታውቋቸዋላችኹ። 21፤በሰማያት፡ያለውን፡የአባቴን፡ፈቃድ፡የሚያደርግ፡እንጂ፥ጌታ፡ሆይ፥ጌታ፡ሆይ፥የሚለኝ፡ዅሉ፡ መንግሥተ፡ሰማያት፡የሚገባ፡አይደለም። 22፤በዚያ፡ቀን፡ብዙዎች፦ጌታ፡ሆይ፥ጌታ፡ሆይ፥በስምኽ፡ትንቢት፡አልተናገርንምን፥በስምኽስ፡አጋንንትን፡ አላወጣንምን፥በስምኽስ፡ብዙ፡ተኣምራትን፡አላደረግንምን፧ይሉኛል። 23፤የዚያን፡ጊዜም፦ከቶ፡አላወቅዃችኹም፤እናንተ፡ዐመፀኛዎች፥ከእኔ፡ራቁ፡ብዬ፡እመሰክርባቸዋለኹ። 24፤ስለዚህ፥ይህን፡ቃሌን፡ሰምቶ፡የሚያደርገው፡ዅሉ፡ቤቱን፡በአለት፡ላይ፡የሠራ፡ልባም፡ሰውን፡ ይመስላል። 25፤ዝናብም፡ወረደ፥ጐርፍም፡መጣ፥ነፋስም፡ነፈሰ፥ያንም፡ቤት፡ገፋው፤በአለት፡ላይም፡ስለ፡ተመሠረተ፡ አልወደቀም። 26፤ይህንም፡ቃሌን፡ሰምቶ፡የማያደርገው፡ሰው፡ዅሉ፡ቤቱን፡በአሸዋ፡ላይ፡የሠራ፡ሰነፍ፡ሰውን፡ይመስላል። 27፤ዝናብም፡ወረደ፥ጐርፍም፡መጣ፥ነፋስም፡ነፈሰ፥ያንም፡ቤት፡መታው፥ወደቀም፤አወዳደቁም፡ታላቅ፡ ኾነ። 28፤ኢየሱስም፡ይህን፡ነገር፡በጨረሰ፡ጊዜ፡ሕዝቡ፡በትምህርቱ፡ተገረሙ፤እንደ፡ጻፊዎቻቸው፡ሳይኾን፡ 29፤እንደ፡ባለሥልጣን፡ያስተምራቸው፡ነበርና።

ምዕራፍ ፰

1፤ከተራራም፡በወረደ፡ጊዜ፡ብዙ፡ሕዝብ፡ተከተሉት። 2፤እንሆም፥ለምጻም፡ቀርቦ፦ጌታ፡ሆይ፥ብትወድስ፡ልታነጻኝ፡ትችላለኽ፡እያለ፡ሰገደለት። 3፤እጁንም፡ዘርግቶ፡ዳሰሰውና፦እወዳለኹ፥ንጻ፡አለው።ወዲያውም፡ለምጹ፡ነጻ። 4፤ኢየሱስም፦ለማንም፡እንዳትናገር፡ተጠንቀቅ፥ነገር፡ግን፥ኼደኽ፡ራስኽን፡ለካህን፡አሳይ፥ለእነርሱም፡ ምስክር፡እንዲኾን፡ሙሴ፡ያዘዘውን፡መባ፡አቅርብ፡አለው። 5፤ወደ፡ቅፍርናሖምም፡በገባ፡ጊዜ፡የመቶ፡አለቃ፡ወደ፡ርሱ፡ቀርቦ፦ጌታ፡ሆይ፥ 6፤ብላቴናዬ፡ሽባ፡ኾኖ፡እጅግ፡እየተሣቀየ፡በቤት፡ተኝቷል፡ብሎ፡ለመነው። 7፤ኢየሱስም፦እኔ፡መጥቼ፡እፈውሰዋለኹ፡አለው። 8፤የመቶ፡አለቃውም፡መልሶ፦ጌታ፡ሆይ፥በቤቴ፡ጣራ፡ከታች፡ልትገባ፡አይገ፟ባ፟ኝም፤ነገር፡ግን፥ቃል፡ ብቻ፡ተናገር፥ብላቴናዬም፡ይፈወሳል። 9፤እኔ፡ደግሞ፡ለሌላዎች፡ተገዢ፡ነኝና፥ከእኔም፡በታች፡ጭፍራ፡አለኝ፤አንዱንም፦ኺድ፡ብለው፡ ይኼዳል፥ሌላውንም፦ና፡ብለው፡ይመጣል፥ባሪያዬንም፦ይህን፡አድርግ፡ብለው፡ያደርጋል፡አለው። 10፤ኢየሱስም፡ሰምቶ፡ተደነቀና፡ለተከተሉት፡እንዲህ፡አለ፦እውነት፡እላችዃለኹ፥በእስራኤል፡እንኳ፡እንዲህ፡ ያለ፡ትልቅ፡እምነት፡አላገኘኹም። 11፤እላችዃለኹም፥ብዙዎች፡ከምሥራቅና፡ከምዕራብ፡ይመጣሉ፡ከአብርሃምና፡ከይሥሐቅ፡ከያዕቆብም፡ጋራ፡ በመንግሥተ፡ሰማያት፡ይቀመጣሉ፤ 12፤የመንግሥት፡ልጆች፡ግን፡በውጭ፡ወዳለው፡ጨለማ፡ይጣላሉ፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡ይኾናል። 13፤ኢየሱስም፡ለመቶ፡አለቃ፦ኺድና፡እንዳመንኽ፡ይኹንልኽ፡አለው።ብላቴናውም፡በዚያች፡ሰዓት፡ ተፈወሰ። 14፤ኢየሱስም፡ወደ፡ጴጥሮስ፡ቤት፡ገብቶ፡ዐማቱን፡በንዳድ፡ታማ፡ተኝታ፡አያት፤ 15፤እጇንም፡ዳሰሰ፥ንዳዱም፡ለቀቃት፤ተነሥታም፡አገለገለቻቸው። 16-17፤በመሸም፡ጊዜ፡አጋንንት፡ያደረባቸውን፡ብዙዎችን፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ፤በነቢዩ፡በኢሳይያስ፦ርሱ፡ ድካማችንን፡ተቀበለ፡ደዌያችንንም፡ተሸከመ፡የተባለው፡ይፈጸም፡ዘንድ፥መናፍስትን፡በቃሉ፡ አወጣ፥የታመሙትንም፡ዅሉ፡ፈወሰ። 18፤ኢየሱስም፡ብዙ፡ሰዎች፡ሲከቡት፡አይቶ፡ወደ፡ማዶ፡እንዲሻገሩ፡አዘዘ። 19፤አንድ፡ጻፊም፡ቀርቦ፦መምህር፡ሆይ፥ወደምትኼድበት፡ዅሉ፡እከተልኻለኹ፡አለው። 20፤ኢየሱስም፦ለቀበሮዎች፡ጕድጓድ፡ለሰማይም፡ወፎች፡መሳፈሪያ፡አላቸው፥ለሰው፡ልጅ፡ግን፡ራሱን፡ የሚያስጠጋበት፡የለውም፡አለው። 21፤ከደቀ፡መዛሙርቱም፡ሌላው፦ጌታ፡ሆይ፥አስቀድሜ፡እንድኼድ፡አባቴን፡እንድቀብር፡ፍቀድልኝ፡ አለው። 22፤ኢየሱስም፦ተከተለኝ፥ሙታናቸውንም፡እንዲቀብሩ፡ሙታንን፡ተዋቸው፡አለው። 23፤ወደ፡ታንኳም፡ሲገባ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ተከተሉት። 24፤እንሆም፥ማዕበሉ፡ታንኳዪቱን፡እስኪደፍናት፡ድረስ፡በባሕር፡ታላቅ፡መናወጥ፡ኾነ፤ርሱ፡ግን፡ተኝቶ፡ ነበር። 25፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ቀርበው፦ጌታ፡ሆይ፥አድነን፥ጠፋን፡እያሉ፡አስነሡት። 26፤ርሱም፦እናንተ፡እምነት፡የጎደላችኹ፥ስለ፡ምን፡ትፈራላችኹ፧አላቸው፤ከዚህ፡በዃላ፡ተነሥቶ፡ ነፋሱንና፡ባሕሩን፡ገሠጸ፥ታላቅ፡ጸጥታም፡ኾነ። 27፤ሰዎቹም፦ነፋሳትና፡ባሕርስ፡ስንኳ፡የሚታዘዙለት፥ይህ፡እንዴት፡ያለ፡ሰው፡ነው፧እያሉ፡ተደነቁ። 28፤ወደ፡ማዶም፡ወደ፡ጌርጋሴኖን፡አገር፡በመጣ፡ጊዜ፥አጋንንት፡ያደሩባቸው፡ኹለት፡ሰዎች፡ከመቃብር፡ ወጥተው፡ተገናኙት፤እነርሱም፡ሰው፡በዚያ፡መንገድ፡ማለፍ፡እስኪሳነው፡ድረስ፡እጅግ፡ክፉዎች፡ነበሩ። 29፤እንሆም፦ኢየሱስ፡ሆይ፥የእግዚአብሔር፡ልጅ፥ከአንተ፡ጋራ፡ምን፡አለን፧ጊዜው፡ሳይደርስ፡ልትሣቅየን፡ ወደዚህ፡መጣኽን፧እያሉ፡ጮኹ። 30፤ከነርሱም፡ርቆ፡የብዙ፡ዕሪያ፡መንጋ፡ይሰማራ፡ነበር። 31፤አጋንንቱም፦ታወጣንስ፡እንደኾንኽ፥ወደዕሪያው፡መንጋ፡ስደደን፡ብለው፡ለመኑት፦ኺዱ፡አላቸው። 32፤እነርሱም፡ወጥተው፡ወደ፡ዕሪያዎቹ፡ኼዱና፡ገቡ፤እንሆም፥የዕሪያዎቹ፡መንጋ፡ዅሉ፡ከአፋፉ፡ወደ፡ ባሕር፡እየተጣደፉ፡ሮጡ፡በውሃም፡ውስጥ፡ሞቱ። 33፤እረኛዎችም፡ሸሹ፥ወደ፡ከተማዪቱም፡ኼደው፡ነገሩን፡ዅሉ፡አጋንንትም፡ባደሩባቸው፡የኾነውን፡አወሩ። 34፤እንሆም፥ከተማው፡ዅሉ፡ኢየሱስን፡ሊገናኝ፡ወጣ፥ባዩትም፡ጊዜ፡ከአገራቸው፡እንዲኼድላቸው፡ ለመኑት።

ምዕራፍ ፱

1፤በታንኳም፡ገብቶ፡ተሻገረና፡ወደገዛ፡ከተማው፡መጣ። 2፤እንሆም፥በዐልጋ፡የተኛ፡ሽባ፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ።ኢየሱስም፡እምነታቸውን፡አይቶ፡ሽባውን፦አንተ፡ ልጅ፥አይዞኽ፥ኀጢአትኽ፡ተሰረየችልኽ፡አለው። 3፤እንሆም፥ከጻፊዎቹ፡አንዳንዱ፡በልባቸው፦ይህስ፡ይሳደባል፡አሉ። 4፤ኢየሱስም፡ዐሳባቸውን፡ዐውቆ፡እንዲህ፡አለ፦ስለ፡ምን፡በልባችኹ፡ክፉ፡ታስባላችኹ፧ 5፤ኀጢአትኽ፡ተሰረየችልኽ፡ከማለት፡ወይስ።ተነሣና፡ኺድ፡ከማለት፡ማናቸው፡ይቀላል፧ 6፤ነገር፡ግን፥በምድር፡ላይ፡ኀጢአትን፡ያስተሰርይ፡ዘንድ፡ለሰው፡ልጅ፡ሥልጣን፡እንዳለው፡ እንድታውቁ፥በዚያን፡ጊዜ፡ሽባውን፦ተነሣ፤ዐልጋኽን፡ተሸከምና፡ወደ፡ቤትኽ፡ኺድ፡አለው። 7፤ተነሥቶም፡ወደ፡ቤቱ፡ኼደ። 8፤ሕዝቡም፡አይተው፡ተደነቁ፥ለሰውም፡እንዲህ፡ያለ፡ሥልጣን፡የሰጠ፡እግዚአብሔርን፡አከበሩ። 9፤ኢየሱስም፡ከዚያ፡ዐልፎ፡በመቅረጫው፡ተቀምጦ፡የነበረ፡ማቴዎስ፡የሚባል፡አንድ፡ሰው፡ አየና፦ተከተለኝ፡አለው።ተነሥቶም፡ተከተለው። 10፤በቤቱም፡በማእዱ፡ተቀምጦ፡ሳለ፥እንሆ፥ብዙ፡ቀራጮችና፡ኀጢአተኛዎች፡መጥተው፡ከኢየሱስና፡ከደቀ፡ መዛሙርቱ፡ጋራ፡ዐብረው፡ተቀመጡ። 11፤ፈሪሳውያንም፡አይተው፡ደቀ፡መዛሙርቱን፦መምህራችኹ፡ከቀራጮችና፡ከኀጢአተኛዎች፡ጋራ፡ዐብሮ፡ ስለ፡ምን፡ይበላል፧አሏቸው። 12፤ኢየሱስም፡ሰምቶ፦ሕመምተኛዎች፡እንጂ፡ባለጤናዎች፡ባለመድኀኒት፡አያስፈልጋቸውም፤ 13፤ነገር፡ግን፥ኼዳችኹ፦ምሕረትን፡እወዳለኹ፡መሥዋዕትንም፡አይደለም፡ያለው፡ምን፡እንደ፡ኾነ፡ ተማሩ፤ኀጢአተኛዎችን፡ወደ፡ንስሓ፡እንጂ፡ጻድቃንን፡ልጠራ፡አልመጣኹምና፡አላቸው። 14፤በዚያን፡ጊዜ፡የዮሐንስ፡ደቀ፡መዛሙርት፡ወደ፡ርሱ፡ቀርበው፦እኛና፡ፈሪሳውያን፥ብዙ፡ጊዜ፡ የምንጦመው፥ደቀ፡መዛሙርትኽ፡ግን፡የማይጦሙት፡ስለ፡ምንድር፡ነው፧አሉት። 15፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አላቸው፦ሚዜዎች፡ሙሽራው፡ከነርሱ፡ጋራ፡ሳለ፡ሊያዝኑ፡ይችላሉን፧ነገር፡ግን፡ሙሽራው፡ከነርሱ፡የሚወሰድበት፡ወራት፡ይመጣል፥በዚያ፡ጊዜም፡ይጦማሉ። 16፤በአረጀ፡ልብስ፡ዐዲስ፡ዕራፊ፡የሚያኖር፡የለም፤መጣፊያው፡ልብሱን፡ይቦጭቀዋልና፥መቀደዱም፡የባሰ፡ ይኾናል። 17፤በአረጀ፡አቍማዳ፡ዐዲስ፡የወይን፡ጠጅ፡የሚያኖር፡የለም፤ቢደረግ፡ግን፥አቍማዳው፡ይፈነዳል፥የወይን፡ ጠጁም፡ይፈሳል፡አቍማዳውም፡ይጠፋል፤ነገር፡ግን፥ዐዲሱን፡የወይን፡ጠጅ፡በዐዲስ፡አቍማዳ፡ ያኖረዋል፥ኹለቱም፡ይጠባበቃሉ። 18፤ይህንም፡ሲነግራቸው፥አንድ፡መኰንን፡መጥቶ፦ልጄ፡አኹን፡ሞተች፤ነገር፡ግን፥መጥተኽ፡እጅኽን፡ ጫንባት፥በሕይወትም፡ትኖራለች፡እያለ፡ሰገደለት። 19፤ኢየሱስም፡ተነሥቶ፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ጋራ፡ተከተለው። 20፤እንሆም፥ከዐሥራ፡ኹለት፡ዓመት፡ዠምሮ፡ደም፡የሚፈሳ፟ት፡ሴት፡በዃላው፡ቀርባ፡የልብሱን፡ጫፍ፡ ዳሰሰች፤ 21፤በልቧ፦ልብሱን፡ብቻ፡የዳሰስኹ፡እንደ፡ኾነ፥እድናለኹ፡ትል፡ነበርና። 22፤ኢየሱስም፡ዘወር፡ብሎ፡አያትና፦ልጄ፡ሆይ፥አይዞሽ፤እምነትሽ፡አድኖሻል፡አላት።ሴቲቱም፡ከዚያች፡ሰዓት፡ዠምራ፡ዳነች። 23፤ኢየሱስም፡ወደመኰንኑ፡ቤት፡በደረሰ፡ጊዜ፥እንቢልተኛዎችንና፡የሚንጫጫውን፡ሕዝብ፡አይቶ፦ 24፤ብላቴናዪቱ፡ተኝታለች፡እንጂ፡አልሞተችምና፡ፈቀቅ፡በሉ፡አላቸው።በጣምም፡ሣቁበት። 25፤ሕዝቡን፡ግን፡ከአስወጡ፡በዃላ፡ገብቶ፡እጇን፡ያዛት፥ብላቴናዪቱም፡ተነሣች። 26፤ያም፡ዝና፡ወደዚያ፡አገር፡ዅሉ፡ወጣ። 27፤ኢየሱስም፡ከዚያ፡ሲያልፍ፡ኹለት፡ዕውሮች፦የዳዊት፡ልጅ፡ሆይ፥ማረን፡ብለው፡እየጮኹ፡ተከተሉት። 28፤ወደ፡ቤትም፡በገባ፡ጊዜ፡ዕውሮቹ፡ወደ፡ርሱ፡ቀረቡ፥ኢየሱስም፦ይህን፡ማድረግ፡እንድችል፡ ታምናላችኹን፧አላቸው፦አዎን፥ጌታ፡ሆይ፡አሉት። 29፤በዚያን፡ጊዜ፦እንደ፡እምነታችኹ፡ይኹንላችኹ፡ብሎ፡ዐይኖቻቸውን፡ዳሰሰ። 30፤ዐይኖቻቸውም፡ተከፈቱ። 31፤ኢየሱስም፦ማንም፡እንዳያውቅ፡ተጠንቀቁ፡ብሎ፡በብርቱ፡አዘዛቸው።እነርሱ፡ግን፡ወጥተው፡በዚያ፡ አገር፡ዅሉ፡ስለ፡ርሱ፡አወሩ። 32፤እነርሱም፡ሲወጡ፥እንሆ፥ጋኔን፡ያደረበትን፡ዲዳ፡ሰው፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ። 33፤ጋኔኑንም፡ካወጣው፡በዃላ፡ዲዳው፡ተናገረ።ሕዝቡም፦እንዲህ፡ያለ፡በእስራኤል፡ዘንድ፡ከቶ፡አልታየም፡ እያሉ፡ተደነቁ። 34፤ፈሪሳውያን፡ግን፦በአጋንንት፡አለቃ፡አጋንንትን፡ያወጣል፡አሉ። 35፤ኢየሱስም፡በምኵራቦቻቸው፡እያስተማረ፥የመንግሥትንም፡ወንጌል፡እየሰበከ፥በሕዝብም፡ያለውን፡ደዌና፡ ሕማም፡ዅሉ፡እየፈወሰ፥በከተማዎችና፡በመንደሮች፡ዅሉ፡ይዞር፡ነበር። 36፤ብዙ፡ሕዝብም፡ባየ፡ጊዜ፥እረኛ፡እንደ፡ሌላቸው፡በጎች፡ተጨንቀው፡ተጥለውም፡ነበርና፥ዐዘነላቸው። 37፤በዚያን፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱን፦መከሩስ፡ብዙ፡ነው፥ሠራተኛዎች፡ግን፡ጥቂቶች፡ናቸው፤ 38፤እንግዲህ፡የመከሩን፡ጌታ፡ወደመከሩ፡ሠራተኛዎች፡እንዲልክ፡ለምኑት፡አላቸው።

ምዕራፍ ፲

1፤ዐሥራ፡ኹለቱን፡ደቀ፡መዛሙርቱን፡ወደ፡ርሱ፡ጠርቶ፥እንዲያወጧቸው፡በርኩሳን፡መናፍስት፡ላይ፡ ደዌንና፡ሕማምንም፡ዅሉ፡እንዲፈውሱ፡ሥልጣን፡ሰጣቸው። 2፤የዐሥራ፡ኹለቱም፡ሐዋርያት፡ስም፡ይህ፡ነው፤መዠመሪያው፡ጴጥሮስ፡የተባለው፡ስምዖን፡ወንድሙ፡ እንድርያስም፥የዘብዴዎስ፡ልጅ፡ያዕቆብም፡ወንድሙ፡ዮሐንስም፥ 3፤ፊልጶስም፡በርተሎሜዎስም፥ቶማስም፡ቀራጩ፡ማቴዎስም፥የእልፍዮስ፡ልጅ፡ያዕቆብም፡ታዴዎስም፡ የተባለው፡ልብድዮስ፥ 4፤ቀነናዊውም፡ስምዖን፡ደግሞም፡አሳልፎ፡የሰጠው፡የአስቆሮቱ፡ይሁዳ። 5፤እነዚህን፡ዐሥራ፡ኹለቱን፡ኢየሱስ፡ላካቸው፥አዘዛቸውም፥እንዲህም፡አለ፦በአሕዛብ፡መንገድ፡ አትኺዱ፥ወደሳምራውያንም፡ከተማ፡አትግቡ፤ 6፤ይልቅስ፡የእስራኤል፡ቤት፡ወደሚኾኑ፡ወደጠፉት፡በጎች፡ኺዱ፡እንጂ። 7፤ኼዳችኹም፦መንግሥተ፡ሰማያት፡ቀርባለች፡ብላችኹ፡ስበኩ። 8፤ድውዮችን፡ፈውሱ፤ሙታንን፡አስነሡ፤ለምጻሞችን፡አንጹ፤አጋንንትን፡አውጡ፤በከንቱ፡ ተቀበላችኹ፥በከንቱ፡ስጡ። 9፤ወርቅ፡ወይም፡ብር፡ወይም፡ናስ፡በመቀነታችኹ፥ 10፤ወይም፡ለመንገድ፡ከረጢት፡ወይም፡ኹለት፡እጀ፡ጠባብ፡ወይም፡ጫማ፡ወይም፡በትር፡ አታግኙ፤ለሠራተኛ፡ምግቡ፡ይገ፟ባ፟ዋልና። 11፤በምትገቡባትም፡በማናቸዪቱም፡ከተማ፡ወይም፡መንደር፥በዚያ፡የሚገባው፡ማን፡እንደ፡ኾነ፡በጥንቃቄ፡ መርምሩ፤እስክትወጡም፡ድረስ፡በዚያ፡ተቀመጡ። 12፤ወደ፡ቤትም፡ስትገቡ፡ሰላምታ፡ስጡ፤ 13፤ቤቱም፡የሚ፟ገ፟ባ፟ው፡ቢኾን፡ሰላማችኹ፡ይድረስለት፤ባይገ፟ባ፟ው፡ግን፡ሰላማችኹ፡ይመለስላችኹ። 14፤ከማይቀበላችኹም፡ቃላችኹንም፡ከማይሰሙ፡ዅሉ፥ከዚያ፡ቤት፡ወይም፡ከዚያች፡ከተማ፡ስትወጡ፡ የእግራችኹን፡ትቢያ፡አራግፉ። 15፤እውነት፡እላችዃለኹ፥በፍርድ፡ቀን፡ከዚያች፡ከተማ፡ይልቅ፡ለሰዶምና፡ለገሞራ፡አገር፡ይቀልላቸዋል። 16፤እንሆ፥እኔ፡እንደ፡በጎች፡በተኵላዎች፡መካከል፡እልካችዃለኹ፤ስለዚህ፥እንደ፡እባብ፡ልባሞች፡እንደ፡ርግብም፡የዋሆች፡ኹኑ። 17፤ነገር፡ግን፥ወደ፡ሸንጎ፡አሳልፈው፡ይሰጧችዃል፥በምኵራቦቻቸውም፡ይገርፏችዃልና፥ከሰዎች፡ተጠበቁ፤ 18፤ለእነርሱና፡ለአሕዛብም፡ምስክር፡እንዲኾን፥ስለ፡እኔ፡ወደ፡ገዢዎች፡ወደ፡ነገሥታትም፡ትወሰዳላችኹ። 19፤አሳልፈውም፡ሲሰጧችኹ፥የምትናገሩት፡በዚያች፡ሰዓት፡ይሰጣችዃልና፥እንዴት፡ወይስ፡ምን፡እንድትናገሩ፡ አትጨነቁ፤ 20፤በእናንተ፡የሚናገር፡የአባታችኹ፡መንፈስ፡ነው፡እንጂ፥የምትናገሩ፡እናንተ፡አይደላችኹምና። 21፤ወንድምም፡ወንድሙን፥አባትም፡ልጁን፡ለሞት፡አሳልፎ፡ይሰጣል፥ልጆችም፡በወላጆቻቸው፡ላይ፡ይነሣሉ፡ ይገድሏቸውማል። 22፤በዅሉም፡ስለ፡ስሜ፡የተጠላችኹ፡ትኾናላችኹ፤እስከ፡መጨረሻ፡የሚጸና፡ግን፡ርሱ፡ይድናል። 23፤በአንዲቱ፡ከተማም፡መከራ፡ቢያሳይዋችኹ፡ወደ፡ሌላዪቱ፡ሽሹ፤እውነት፡እላችዃለኹና፥የሰው፡ልጅ፡ እስኪመጣ፡ድረስ፡የእስራኤልን፡ከተማዎች፡አትዘልቁም። 24፤ደቀ፡መዝሙር፡ከመምህሩ፥ባሪያም፡ከጌታው፡አይበልጥም። 25፤ደቀ፡መዝሙር፡እንደ፡መምህሩ፥ባሪያም፡እንደ፡ጌታው፡መኾኑ፡ይበቃዋል።ባለቤቱን፡ብዔል፡ዜቡል፡ ካሉት፥ቤተ፡ሰዎቹንማ፡እንዴት፡አብዝተው፡አይሏቸው! 26፤እንግዲህ፡አትፍሯቸው፤የማይገለጥ፡የተከደነ፥የማይታወቅም፡የተሰወረ፡ምንም፡የለምና። 27፤በጨለማ፡የምነግራችኹን፡በብርሃን፡ተናገሩ፤በዦሮም፡የምትሰሙትን፡በሰገነት፡ላይ፡ስበኩ። 28፤ሥጋንም፡የሚገድሉትን፡ነፍስን፡ግን፡መግደል፡የማይቻላቸውን፡አትፍሩ፤ይልቅስ፡ነፍስንም፡ሥጋንም፡ በገሃነም፡ሊያጠፋ፡የሚቻለውን፡ፍሩ። 29፤ኹለት፡ድንቢጦች፡በዐምስት፡ሳንቲም፡ይሸጡ፡የለምን፧ከነርሱም፡አንዲቱ፡ያለአባታችኹ፡ፈቃድ፡ በምድር፡ላይ፡አትወድቅም። 30፤የእናንተስ፡የራሳችኹ፡ጠጕር፡ዅሉ፡እንኳ፡ተቈጥሯል። 31፤እንግዲህ፡አትፍሩ፡ከብዙ፡ድንቢጦች፡እናንተ፡ትበልጣላችኹ። 32፤ስለዚህ፥በሰው፡ፊት፡ለሚመሰክርልኝ፡ዅሉ፥እኔ፡ደግሞ፡በሰማያት፡ባለው፡በአባቴ፡ፊት፡ እመሰክርለታለኹ፤ 33፤በሰው፡ፊትም፡የሚክደኝን፡ዅሉ፡እኔ፡ደግሞ፡በሰማያት፡ባለው፡በአባቴ፡ፊት፡እክደዋለኹ። 34፤በምድር፡ላይ፡ሰላምን፡ለማምጣት፡የመጣኹ፡አይምሰላችኹ፤ሰይፍን፡እንጂ፡ሰላምን፡ለማምጣት፡ አልመጣኹም። 35፤ሰውን፡ከአባቱ፥ሴት፡ልጅንም፡ከእናቷ፥ምራትንም፡ከአማቷ፡እለያይ፡ዘንድ፡መጥቻለኹና፤ 36፤ለሰውም፡ቤተ፡ሰዎቹ፡ጠላቶች፡ይኾኑበታል። 37፤ከእኔ፡ይልቅ፡አባቱን፡ወይም፡እናቱን፡የሚወድ፡ለእኔ፡ሊኾን፡አይገ፟ባ፟ውም፤ከእኔ፡ይልቅም፡ወንድ፡ ልጁን፡ወይም፡ሴት፡ልጁን፡የሚወድ፡ለእኔ፡ሊኾን፡አይገ፟ባ፟ውም፤ 38፤መስቀሉንም፡የማይዝ፡በዃላዬም፡የማይከተለኝ፡ለእኔ፡ሊኾን፡አይገ፟ባ፟ውም። 39፤ነፍሱን፡የሚያገኝ፡ያጠፋታል፥ነፍሱንም፡ስለ፡እኔ፡የሚያጠፋ፡ያገኛታል። 40፤እናንተን፡የሚቀበል፡እኔን፡ይቀበላል፥እኔንም፡የሚቀበል፡የላከኝን፡ይቀበላል። 41፤ነቢይን፡በነቢይ፡ስም፡የሚቀበል፡የነቢይን፡ዋጋ፡ይወስዳል፥ጻድቅንም፡በጻድቅ፡ስም፡የሚቀበል፡የጻድቁን፡ ዋጋ፡ይወስዳል። 42፤ማንም፡ከነዚህ፡ከታናናሾቹ፡ለአንዱ፡ቀዝቃዛ፡ጽዋ፡ውሃ፡ብቻ፡በደቀ፡መዝሙር፡ስም፡የሚያጠጣ፥እውነት፡እላችዃለኹ፥ዋጋው፡አይጠፋበትም።

ምዕራፍ ፲፩

1፤ኢየሱስም፡ዐሥራ፡ኹለቱን፡ደቀ፡መዛሙርቱን፡ማዘዝ፡በፈጸመ፡ጊዜ፡በከተማዎቻቸው፡ሊያስተምርና፡ ሊሰብክ፡ከዚያ፡ዐለፈ። 2፤ዮሐንስም፡በወህኒ፡ሳለ፡የክርስቶስን፡ሥራ፡ሰምቶ፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ኹለት፡ላከና። 3፤የሚመጣው፡አንተ፡ነኽን፧ወይስ፡ሌላ፡እንጠብቅ፧አለው። 4፤ኢየሱስም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦ኼዳችኹ፡ያያችኹትን፡የሰማችኹትንም፡ለዮሐንስ፡አውሩለት፤5፤ዕውሮች፡ያያሉ፡ዐንካሳዎችም፡ይኼዳሉ፥ለምጻሞችም፡ይነጻሉ፡ደንቈሮዎችም፡ይሰማሉ፥ሙታንም፡ይነሣሉ፡ 6፤ለድኻዎችም፡ወንጌል፡ይሰበካል፤በእኔም፡የማይሰናከለው፡ዅሉ፡ብፁዕ፡ነው። 7፤እነዚያም፡ሲኼዱ፡ኢየሱስ፡ለሕዝቡ፡ስለ፡ዮሐንስ፡ሊናገር፡ዠመረ፥እንዲህም፡አለ፦ምን፡ልታዩ፡ወደ፡ ምድረ፡በዳ፡ወጣችኹ፧ 8፤ነፋስ፡የሚወዘውዘውን፡ሸምበቆን፧ወይስ፡ምን፡ልታዩ፡ወጣችኹ፧ቀጭን፡ልብስ፡የለበሰ፡ ሰውን፧እንሆ፥ቀጭን፡ልብስ፡የለበሱ፡በነገሥታት፡ቤት፡አሉ። 9፤ወይስ፡ምን፡ልታዩ፡ወጣችኹ፧ነቢይን፧አዎን፡እላችዃለኹ፥ከነቢይም፡የሚበልጠውን። 10፤እንሆ፥መንገድኽን፡በፊትኽ፡የሚጠርግ፡መልክተኛዬን፡በፊትኽ፡እልካለኹ፡ተብሎ፡የተጻፈለት፡ይህ፡ ነውና። 11፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ከሴቶች፡ከተወለዱት፡መካከል፡ከመጥምቁ፡ዮሐንስ፡የሚበልጥ፡ አልተነሣም፤በመንግሥተ፡ሰማያት፡ግን፡ከዅሉ፡የሚያንሰው፡ይበልጠዋል። 12፤ከመጥምቁም፡ከዮሐንስ፡ዘመን፡ዠምሮ፡እስከ፡ዛሬ፡ድረስ፡መንግሥተ፡ሰማያት፡ትገፋለች፥ግፈኛዎችም፡ ይናጠቋታል። 13፤ነቢያት፡ዅሉና፡ሕጉ፡እስከ፡ዮሐንስ፡ድረስ፡ትንቢት፡ተናገሩ፤ 14፤ልትቀበሉትስ፡ብትወዱ፥ይመጣ፡ዘንድ፡ያለው፡ኤልያስ፡ይህ፡ነው። 15፤የሚሰማ፡ዦሮ፡ያለው፡ይስማ። 16፤ነገር፡ግን፥ይህን፡ትውልድ፡በምን፡እመስለዋለኹ፧በገበያ፡የሚቀመጡትን፡ልጆች፡ይመስላሉ፥እነርሱም፡ ባልንጀራዎቻቸውን፡እየጠሩ። 17፤እንቢልታ፡ነፋንላችኹ፥ዘፈንም፡አልዘፈናችኹም፤ሙሾ፡አወጣንላችኹ፥ዋይ፡ዋይም፡አላላችኹም፡ ይሏቸዋል። 18፤ዮሐንስ፡ሳይበላና፡ሳይጠጣ፡መጣ፥እነርሱም፦ጋኔን፡አለበት፡አሉት። 19፤የሰው፡ልጅ፡እየበላና፡እየጠጣ፡መጣ፥እነርሱም፦እንሆ፥በላተኛና፡የወይን፡ጠጅ፡ጠጪ፥የቀራጮችና፡ የኀጢአተኛዎች፡ወዳጅ፡ይሉታል።ጥበብም፡በልጆቿ፡ጸደቀች። 20፤በዚያን፡ጊዜ፡የሚበዙ፡ተኣምራት፡የተደረገባቸውን፡ከተማዎች፡ንስሓ፡ስላልገቡ፡ሊነቅፋቸው፡ዠመረ፡ እንዲህም፡አለ፦ 21፤ወዮልሽ፡ኮራዚ፤ወዮልሽ፡ቤተ፡ሳይዳ፤በእናንተ፡የተደረገው፡ተኣምራት፡በጢሮስና፡በሲዶና፡ተደርጎ፡ቢኾን፥ማቅ፡ለብሰው፡ዐመድም፡ነስንሰው፡ከብዙ፡ጊዜ፡በፊት፡ንስሓ፡በገቡ፡ነበርና። 22፤ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥በፍርድ፡ቀን፡ከእናንተ፡ይልቅ፡ለጢሮስና፡ለሲዶና፡ይቀልላቸዋል። 23፤አንቺም፡ቅፍርናሖም፥እስከ፡ሰማይ፡ከፍ፡አልሽን፧ወደ፡ሲኦል፡ትወርጃለሽ፤ባንቺ፡የተደረገው፡ ተኣምራት፡በሰዶም፡ተደርጎ፡ቢኾን፥እስከ፡ዛሬ፡በኖረች፡ነበርና። 24፤ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥በፍርድ፡ቀን፡ከአንቺ፡ይልቅ፡ለሰዶም፡አገር፡ይቀልላታል። 25፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡መልሶ፡እንዲህ፡አለ፦አባት፡ሆይ፥የሰማይና፡የምድር፡ጌታ፥ይህን፡ ከጥበበኛዎችና፡ከአስተዋዮች፡ሰውረኽ፡ለሕፃናት፡ስለ፡ገለጥኽላቸው፡አመሰግንኻለኹ፤ 26፤አዎን፥አባት፡ሆይ፥ፈቃድኽ፡በፊትኽ፡እንዲህ፡ኾኗልና። 27፤ዅሉ፡ከአባቴ፡ዘንድ፡ተሰጥቶኛል፤ከአብ፡በቀር፡ወልድን፡የሚያውቅ፡የለም፥ከወልድም፡በቀር፡ወልድም፡ ሊገለጥለት፡ከሚፈቅድ፡በቀር፡አብን፡የሚያውቅ፡የለም። 28፤እናንተ፡ደካማዎች፡ሸክማችኹ፡የከበደ፡ዅሉ፥ወደ፡እኔ፡ኑ፥እኔም፡አሳርፋችዃለኹ። 29፤ቀንበሬን፡በላያችኹ፡ተሸከሙ፡ከእኔም፡ተማሩ፥እኔ፡የዋህ፡በልቤም፡ትሑት፡ነኝና፥ለነፍሳችኹም፡ ዕረፍት፡ታገኛላችኹ፤ 30፤ቀንበሬ፡ልዝብ፡ሸክሜም፡ቀሊል፡ነውና።

ምዕራፍ ፲፪

1፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡በሰንበት፡ቀን፡በዕርሻ፡መካከል፡ዐለፈ፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ተራቡና፡እሸት፡ ይቀጥፉ፡ይበሉም፡ዠመር። 2፤ፈሪሳውያንም፡አይተው፦እንሆ፥ደቀ፡መዛሙርትኽ፡በሰንበት፡ማድረግ፡ያልተፈቀደውን፡ያደርጋሉ፡አሉት። 3-4፤ርሱ፡ግን፡እንዲህ፡አላቸው፦ዳዊትና፡ከርሱ፡ጋራ፡የነበሩት፡በተራቡ፡ጊዜ፥ርሱ፡ ያደረገውን፥ወደእግዚአብሔር፡ቤት፡እንደ፡ገባ፡ካህናትም፡ብቻ፡እንጂ፡ርሱና፡ከርሱ፡ጋራ፡የነበሩት፡ሊበሉት፡ ያልተፈቀደውን፡የመሥዋዕቱን፡ኅብስት፡እንደ፡በላ፡አላነበባችኹምን፧ 5፤ካህናትም፡በሰንበት፡በመቅደስ፡ሰንበትን፡እንዲያረክሱ፡ኀጢአትም፡እንዳይኾንባቸው፡በሕጉ፡ አላነበባችኹምን፧ 6፤ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥ከመቅደስ፡የሚበልጥ፡ከዚህ፡አለ። 7፤ምሕረትን፡እወዳለኹ፡መሥዋዕትንም፡አይደለም፡ያለው፡ምን፡እንደ፡ኾነ፡ብታውቁስ፡ኀጢአት፡ የሌለባቸውን፡ባልኰነናችኹም፡ነበር። 8፤የሰው፡ልጅ፡የሰንበት፡ጌታ፡ነውና። 9፤ከዚያም፡ዐልፎ፡ወደ፡ምኵራባቸው፡ገባ። 10፤እንሆም፥እጁ፡የሰለለች፡ሰው፡ነበረ፤ይከሱትም፡ዘንድ።በሰንበት፡መፈወስ፡ተፈቅዷልን፧ብለው፡ ጠየቁት። 11፤ርሱ፡ግን፦ከእናንተ፡አንድ፡በግ፡ያለው፡በሰንበት፡በጕድጓድ፡ቢወድቅበት፥ይዞ፡የማያወጣው፡ሰው፡ ማን፡ነው፧ 12፤እንግዲህ፡ሰው፡ከበግ፡ይልቅ፡እንደምን፡አይበልጥም! ስለዚህ፡በሰንበት፡መልካም፡መሥራት፡ተፈቅዷል፡ አላቸው። 13፤ከዚያም፡በዃላ፡ሰውየውን፦እጅኽን፡ዘርጋ፡አለው።ዘረጋትም፥እንደ፡ኹለተኛዪቱም፡ደኅና፡ኾነች። 14፤ፈሪሳውያን፡ግን፡ወጥተው፡እንዴት፡አድርገው፡እንዲያጠፉት፡ተማከሩበት። 15፤ኢየሱስም፡ዐውቆ፡ከዚያ፡ፈቀቅ፡አለ።ብዙ፡ሰዎችም፡ተከተሉት፥ዅሉንም፡ፈወሳቸው፥እንዳይገልጡትም፡ አዘዛቸው፤ 16-17፤በነቢዩ፡በኢሳይያስ፡የተባለው፡ይፈጸም፡ዘንድ፡እንዲህ፡ሲል፦ 18፤እንሆ፥የመረጥኹት፡ብላቴናዬ፥ነፍሴ፡ደስ፡የተሠኘችበት፡ወዳጄ፤መንፈሴን፡በርሱ፡ላይ፡ አኖራለኹ፥ፍርድንም፡ለአሕዛብ፡ያወራል። 19፤አይከራከርም፡አይጮኽምም፥ድምፁንም፡በአደባባይ፡የሚሰማ፡የለም። 20፤ፍርድን፡ድል፡ለመንሣት፡እስኪያወጣ፥የተቀጠቀጠን፡ሸምበቆ፡አይሰብርም፡የሚጤስን፡የጧፍ፡ክርም፡ አያጠፋም። 21፤አሕዛብም፡በስሙ፡ተስፋ፡ያደርጋሉ። 22፤ከዚህም፡በዃላ፡ጋኔን፡ያደረበትን፡ዕውር፡ዲዳም፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ፤ዕውሩም፡ዲዳውም፡እስኪያይና፡ እስኪናገር፡ድረስ፡ፈወሰው። 23፤ሕዝቡም፡ዅሉ፡ተገረሙና፦እንጃ፥ይህ፡ሰው፡የዳዊት፡ልጅ፡ይኾንን፧አሉ። 24፤ፈሪሳውያን፡ግን፡ሰምተው፦ይህ፡በብዔል፡ዜቡል፡በአጋንንት፡አለቃ፡ካልኾነ፡በቀር፡አጋንንትን፡ አያወጣም፡አሉ። 25፤ኢየሱስ፡ግን፡ዐሳባቸውን፡ዐውቆ፡እንዲህ፡አላቸው፦ርስ፡በርሷ፡የምትለያይ፡መንግሥት፡ዅላ፡ ትጠፋለች፥ርስ፡በርሱ፡የሚለያይ፡ከተማም፡ዅሉ፡ወይም፡ቤት፡አይቆምም። 26፤ሰይጣንም፡ሰይጣንን፡የሚያወጣ፡ከኾነ፥ርስ፡በርሱ፡ተለያየ፥እንግዲህ፡መንግሥቱ፡እንዴት፡ትቆማለች፧ 27፤እኔስ፡በብዔል፡ዜቡል፡አጋንንትን፡የማወጣ፡ከኾንኹ፥ልጆቻችኹ፡በማን፡ያወጧቸዋል፧ስለዚህ፡እነርሱ፡ ፈራጆች፡ይኾኑባችዃል። 28፤እኔ፡ግን፡በእግዚአብሔር፡መንፈስ፡አጋንንትን፡የማወጣ፡ከኾንኹ፥እንግዲህ፡የእግዚአብሔር፡መንግሥት፡ ወደ፡እናንተ፡ደርሳለች። 29፤ወይስ፡ሰው፡አስቀድሞ፡ኀይለኛውን፡ሳያስር፡ወደኀይለኛው፡ቤት፡ገብቶ፡ዕቃውን፡ሊነጥቀው፡እንዴት፡ ይችላል፧ከዚያም፡ወዲያ፡ቤቱን፡ይበዘብዛል። 30፤ከእኔ፡ጋራ፡ያልኾነ፡ይቃወመኛል፥ከእኔ፡ጋራም፡የማያከማች፡ይበትናል። 31፤ስለዚህ፥እላችዃለኹ፥ኀጢአትና፡ስድብ፡ዅሉ፡ለሰዎች፡ይሰረይላቸዋል፥ነገር፡ግን፥መንፈስ፡ቅዱስን፡ ለሰደበ፡አይሰረይለትም። 32፤በሰው፡ልጅ፡ላይ፡ቃል፡የሚናገር፡ዅሉ፡ይሰረይለታል፤በመንፈስ፡ቅዱስ፡ላይ፡ግን፡የሚናገር፡ዅሉ፡ በዚህ፡ዓለም፡ቢኾን፡ወይም፡በሚመጣው፡አይሰረይለትም። 33፤ዛፍ፡ከፍሬዋ፡ትታወቃለችና፡ዛፏን፡መልካም፥ፍሬዋንም፡መልካም፡አድርጉ፥ወይም፡ዛፏን፡ክፉ፡ ፍሬዋንም፡ክፉ፡አድርጉ። 34፤እናንተ፡የእፍኝት፡ልጆች፥ክፉዎች፡ስትኾኑ፡መልካም፡ለመናገር፡እንዴት፡ትችላላችኹ፧በልብ፡ሞልቶ፡ ከተረፈው፡አፍ፡ይናገራልና። 35፤መልካም፡ሰው፡ከልቡ፡መልካም፡መዝገብ፡መልካም፡ነገርን፡ያወጣል፥ክፉ፡ሰውም፡ከክፉ፡መዝገብ፡ ክፉ፡ነገርን፡ያወጣል። 36፤እኔ፡እላችዃለኹ፥ሰዎች፡ስለሚናገሩት፡ስለ፡ከንቱ፡ነገር፡ዅሉ፡በፍርድ፡ቀን፡መልስ፡ይሰጡበታል፤ 37፤ከቃልኽ፡የተነሣ፡ትጸድቃለኽና፡ከቃልኽም፡የተነሣ፡ትኰነናለኽ። 38፤በዚያን፡ጊዜ፡ከጻፊዎችና፡ከፈሪሳውያን፡አንዳንዶቹ፡መለሱና፦መምህር፡ሆይ፥ከአንተ፡ምልክት፡ እንድናይ፡እንወዳለን፡አሉ። 39፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦ክፉና፡አመንዝራ፡ትውልድ፡ምልክት፡ይሻል፥ከነቢዩም፡ከዮናስ፡ ምልክት፡በቀር፡ምልክት፡አይሰጠውም። 40፤ዮናስ፡በዓሣ፡ዐንበሪ፡ሆድ፡ሦስት፡ቀንና፡ሦስት፡ሌሊት፡እንደ፡ነበረ፥እንዲሁ፡የሰው፡ልጅ፡በምድር፡ ልብ፡ሦስት፡ቀንና፡ሦስት፡ሌሊት፡ይኖራል። 41፤የነነዌ፡ሰዎች፡በፍርድ፡ቀን፡ከዚህ፡ትውልድ፡ጋራ፡ተነሥተው፡ይፈርዱበታል፤በዮናስ፡ስብከት፡ንስሓ፡ ገብተዋልና፥እንሆም፥ከዮናስ፡የሚበልጥ፡ከዚህ፡አለ። 42፤ንግሥተ፡አዜብ፡በፍርድ፡ቀን፡ከዚህ፡ትውልድ፡ጋራ፡ተነሥታ፡ትፈርድበታለች፤የሰሎሞንን፡ጥበብ፡ ለመስማት፡ከምድር፡ዳር፡መጥታለችና፥እንሆም፥ከሰሎሞን፡የሚበልጥ፡ከዚህ፡አለ። 43፤ርኩስ፡መንፈስ፡ግን፡ከሰው፡በወጣ፡ጊዜ፥ዕረፍት፡እየፈለገ፡ውሃ፡በሌለበት፡ቦታ፡ያልፋል፥አያገኝምም። 44፤በዚያን፡ጊዜም፦ወደወጣኹበት፡ቤቴ፡እመለሳለኹ፡ይላል፤ቢመጣም፡ባዶ፡ኾኖ፡ተጠርጎና፡አጊጦ፡ ያገኘዋል። 45፤ከዚያ፡ወዲያ፡ይኼድና፡ከርሱ፡የከፉትን፡ሰባት፡ሌላዎችን፡አጋንንት፡ከርሱ፡ጋራ፡ይወስዳል፥ገብተውም፡ በዚያ፡ይኖራሉ፤ለዚያም፡ሰው፡ከፊተኛው፡ይልቅ፡የዃለኛው፡ይብስበታል።ለዚህ፡ክፉ፡ትውልድ፡ደግሞ፡ እንዲሁ፡ይኾንበታል። 46፤ገናም፡ለሕዝቡ፡ሲናገር፥እንሆ፥እናቱና፡ወንድሞቹ፡ሊነጋገሩት፡ፈልገው፡በውጭ፡ቆመው፡ነበር። 47፤አንዱም፦እንሆ፥እናትኽና፡ወንድሞችኽ፡ሊነጋገሩኽ፡ፈልገው፡በውጭ፡ቆመዋል፡አለው። 48፤ርሱ፡ግን፡ለነገረው፡መልሶ፦እናቴ፡ማን፡ናት፧ወንድሞቼስ፡እነማን፡ናቸው፧አለው። 49፤እጁንም፡ወደ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ዘርግቶ፦እንሆ፥እናቴና፡ወንድሞቼ፤ 50፤በሰማያት፡ያለውን፡የአባቴን፡ፈቃድ፡የሚያደርግ፡ዅሉ፥ርሱ፡ወንድሜ፡እኅቴም፡እናቴም፡ነውና፥አለ።

ምዕራፍ ፲፫

1፤በዚያን፡ቀን፡ኢየሱስ፡ከቤት፡ወጥቶ፡በባሕር፡አጠገብ፡ተቀመጠ፤ 2፤ርሱም፡በታንኳ፡ገብቶ፡እስኪቀመጥ፡ድረስ፡ብዙ፡ሰዎች፡ወደ፡ርሱ፡ተሰበሰቡ፥ሕዝቡም፡ዅሉ፡በወደቡ፡ቆመው፡ነበር። 3፤በምሳሌም፡ብዙ፡ነገራቸው፡እንዲህም፡አላቸው፦እንሆ፥ዘሪ፡ሊዘራ፡ወጣ። 4፤ርሱም፡ሲዘራ፡አንዳንዱ፡በመንገድ፡ዳር፡ወደቀ፥ወፎችም፡መጥተው፡በሉት። 5፤ሌላውም፡ብዙ፡መሬት፡በሌለበት፡በጭንጫ፡ላይ፡ወደቀ፤ጥልቅ፡መሬትም፡ስላልነበረው፡ወዲያው፡በቀለ፥ 6፤ፀሓይ፡በወጣ፡ጊዜ፡ግን፡ጠወለገ፥ሥርም፡ስላልነበረው፡ደረቀ። 7፤ሌላውም፡በሾኽ፡መካከል፡ወደቀ፥ሾኽም፡ወጣና፡ዐነቀው። 8፤ሌላውም፡በመልካም፡መሬት፡ወደቀ፤አንዱም፡መቶ፥አንዱም፡ስድሳ፥አንዱም፡ሠላሳ፡ፍሬ፡ሰጠ። 9፤የሚሰማ፡ዦሮ፡ያለው፡ይስማ። 10፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ቀርበው፦ስለ፡ምን፡በምሳሌ፡ትነግራቸዋለኽ፧አሉት። 11፤ርሱም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦ለእናንተ፡የመንግሥተ፡ሰማያትን፡ምስጢር፡ማወቅ፡ ተሰጥቷችዃል፥ለእነርሱ፡ግን፡አልተሰጣቸውም። 12፤ላለው፡ይሰጠዋልና፥ይበዛለትማል፤ከሌለው፡ግን፡ያው፡ያለው፡እንኳ፡ይወሰድበታል። 13፤ስለዚህ፥እያዩ፡ስለማያዩ፥እየሰሙም፡ስለማይሰሙ፥ስለማያስተውሉም፡በምሳሌ፡እነግራቸዋለኹ። 14፤መስማት፡ትሰማላችኹና፡አታስተውሉም፥ማየትም፡ታያላችኹና፡አትመለከቱም። 15፤በዐይናቸው፡እንዳያዩ፥በዦሯቸውም፡እንዳይሰሙ፥በልባቸውም፡እንዳያስተውሉ፥ተመልሰውም፡ እንዳልፈውሳቸው፥የዚህ፡ሕዝብ፡ልብ፡ደንድኗልና፥ዦሯቸውም፡ደንቍሯል፥ዐይናቸውንም፡ጨፍነዋል፡የሚል፡ የኢሳይያስ፡ትንቢት፡በእነርሱ፡ይፈጸማል። 16፤የእናንተ፡ግን፡ዐይኖቻችኹ፡ስለሚያዩ፡ዦሮዎቻችኹም፡ስለሚሰሙ፡ብፁዓን፡ናቸው። 17፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ብዙዎች፡ነቢያትና፡ጻድቃን፡የምታዩትን፡ሊያዩ፡ተመኝተው፡ አላዩም፥የምትሰሙትንም፡ሊሰሙ፡ተመኝተው፡አልሰሙም። 18፤እንግዲህ፡እናንተ፡የዘሪውን፡ምሳሌ፡ስሙ። 19፤የመንግሥትን፡ቃል፡ሰምቶ፡በማያስተውል፡ዅሉ፥ክፉው፡ይመጣል፥በልቡ፡የተዘራውንም፡ ይነጥቃል፤በመንገድ፡ዳር፡የተዘራው፡ይህ፡ነው። 20፤በጭንጫ፡ላይ፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡ሰምቶ፡ወዲያው፡በደስታ፡የሚቀበለው፡ነው፤ 21፤ነገር፡ግን፥ለጊዜው፡ነው፡እንጂ፡በርሱ፡ሥር፡የለውም፥በቃሉ፡ምክንያትም፡መከራ፡ወይም፡ስደት፡ በኾነ፡ጊዜ፡ወዲያው፡ይሰናከላል። 22፤በሾኽ፡መካከል፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡የሚሰማ፡ነው፥የዚህም፡ዓለም፡ዐሳብና፡የባለጠግነት፡ መታለል፡ቃሉን፡ያንቃል፥የማያፈራም፡ይኾናል። 23፤በመልካም፡መሬት፡የተዘራውም፡ይህ፡ቃሉን፡ሰምቶ፡የሚያስተውል፡ነው፤ርሱም፡ፍሬ፡ያፈራል፡ አንዱም፡መቶ፡አንዱም፡ስድሳ፡አንዱም፡ሠላሳ፡ያደርጋል። 24፤ሌላ፡ምሳሌ፡አቀረበላቸው፡እንዲህም፡አለ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡በዕርሻው፡መልካም፡ዘርን፡የዘራን፡ ሰው፡ትመስላለች። 25፤ሰዎቹ፡ሲተኙ፡ግን፡ጠላቱ፡መጣና፡በስንዴው፡መካከል፡እንክርዳድን፡ዘርቶ፡ኼደ። 26፤ስንዴውም፡በበቀለና፡ባፈራ፡ጊዜ፥እንክርዳዱ፡ደግሞ፡ያን፡ጊዜ፡ታየ። 27፤የባለቤቱም፡ባሪያዎች፡ቀርበው፦ጌታ፡ሆይ፥መልካምን፡ዘር፡በዕርሻኽ፡ዘርተኽ፡ አልነበርኽምን፧እንክርዳዱንስ፡ከወዴት፡አገኘ፧አሉት። 28፤ርሱም፦ጠላት፡ይህን፡አደረገ፡አላቸው።ባሮቹም፦እንግዲህ፡ኼደን፡ብንለቅመው፡ትወዳለኽን፧አሉት። 29፤ርሱ፡ግን፦እንክርዳዱን፡ስትለቅሙ፡ስንዴውን፡ከርሱ፡ጋራ፡እንዳትነቅሉት፡አይኾንም። 30፤ተዉአቸው፤እስከ፡መከር፡ጊዜ፡ዐብረው፡ይደጉ፤በመከር፡ጊዜም፡ዐጫጆችን፦እንክርዳዱን፡ አስቀድማችኹ፡ልቀሙ፡በእሳትም፡ለማቃጠል፡በየነዶው፡እሰሩ፥ስንዴውን፡ግን፡በጐተራዬ፡ክተቱ፡እላለኹ፡ አለ። 31፤ሌላ፡ምሳሌ፡አቀረበላቸው፡እንዲህም፡አለ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡ሰው፡ወስዶ፡በዕርሻው፡የዘራትን፡ የሰናፍጭ፡ቅንጣት፡ትመስላለች፤ 32፤ርሷም፡ከዘር፡ዅሉ፡ታንሳለች፥ባደገች፡ጊዜ፡ግን፥ከአታክልቶች፡ትበልጣለች፡የሰማይም፡ወፎች፡ መጥተው፡በቅርንጫፎቿ፡እስኪሰፍሩ፡ድረስ፡ዛፍ፡ትኾናለች። 33፤ሌላ፡ምሳሌ፡ነገራቸው፡እንዲህም፡አለ፦መንግሥተ፡ሰማያት፡ዅሉ፡እስኪቦካ፡ድረስ፡ሴት፡ወስዳ፡ በሦስት፡መስፈሪያ፡ዱቄት፡የሸሸገችውን፡ርሾ፡ትመስላለች። 34-35፤ኢየሱስም፡ለሕዝቡ፡ይህን፡ዅሉ፡በምሳሌ፡ተናገረ፤በነቢዩም፦በምሳሌ፡አፌን፡እከፍታለኹ፥ዓለም፡ ከተፈጠረ፡ዠምሮ፡የተሰወረውንም፡እናገራለኹ፡የተባለው፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ያለምሳሌ፡አልተናገራቸውም። 36፤በዚያን፡ጊዜ፡ሕዝቡን፡ትቶ፡ወደ፡ቤት፡ገባ።ደቀ፡መዛሙርቱም፡ወደ፡ርሱ፡ቀርበው፦የዕርሻውን፡ እንክርዳድ፡ምሳሌ፡ተርጕምልን፡አሉት። 37፤ርሱም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦መልካምን፡ዘር፡የዘራው፡የሰው፡ልጅ፡ነው፤ዕርሻውም፡ዓለም፡ነው፤ 38፤መልካሙም፡ዘር፡የመንግሥት፡ልጆች፡ናቸው፤ 39፤እንክርዳዱም፡የክፉው፡ልጆች፡ናቸው፥የዘራውም፡ጠላት፡ዲያብሎስ፡ነው፤መከሩም፡የዓለም፡መጨረሻ፡ ነው፥ዐጫጆችም፡መላእክት፡ናቸው። 40፤እንግዲህ፡እንክርዳድ፡ተለቅሞ፡በእሳት፡እንደሚቃጠል፥በዓለም፡መጨረሻ፡እንዲሁ፡ይኾናል። 41፤የሰው፡ልጅ፡መላእክቱን፡ይልካል፥ከመንግሥቱም፡እንቅፋትን፡ዅሉ፡ዐመፃንም፡የሚያደርጉትን፡ ይለቅማሉ፥ 42፤ወደ፡እቶነ፡እሳትም፡ይጥሏቸዋል፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡ይኾናል። 43፤በዚያን፡ጊዜ፡ጻድቃን፡በአባታቸው፡መንግሥት፡እንደ፡ፀሓይ፡ይበራሉ።የሚሰማ፡ዦሮ፡ያለው፡ይስማ። 44፤ደግሞ፡መንግሥተ፡ሰማያት፡በዕርሻ፡ውስጥ፡የተሰወረውን፡መዝገብ፡ትመስላለች፤ሰውም፡አግኝቶ፡ ሰወረው፥ከደስታውም፡የተነሣ፡ኼዶ፡ያለውን፡ዅሉ፡ሸጠና፡ያን፡ዕርሻ፡ገዛ። 45፤ደግሞ፡መንግሥተ፡ሰማያት፡መልካምን፡ዕንቍ፡የሚሻ፡ነጋዴን፡ትመስላለች፤ 46፤ዋጋዋም፡እጅግ፡የበዛ፡አንዲት፡ዕንቍ፡በአገኘ፡ጊዜ፡ኼዶ፡ያለውን፡ዅሉ፡ሸጠና፡ገዛት። 47፤ደግሞ፡መንግሥተ፡ሰማያት፡ወደ፡ባሕር፡የተጣለች፡ከዅሉም፡ዐይነት፡የሰበሰበች፡መረብን፡ትመስላለች፤ 48፤በሞላችም፡ጊዜ፡ወደ፡ወደቡ፡አወጧት፥ተቀምጠውም፡መልካሙን፡ለቅመው፡በዕቃዎች፡ውስጥ፡ አከማቹ፡ክፉውን፡ግን፡ወደ፡ውጭ፡ጣሉት። 49፤በዓለም፡መጨረሻ፡እንዲሁ፡ይኾናል፤መላእክት፡መጥተው፡ኀጢአተኛዎችን፡ከጻድቃን፡መካከል፡ ይለይዋቸዋል፥ወደ፡እቶነ፡እሳትም፡ይጥሏቸዋል፤ 50፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡ይኾናል። 51፤ኢየሱስም፦ይህን፡ዅሉ፡አስተዋላችኹን፧አላቸው፦አዎን፡አሉት። 52፤ርሱም፦ስለዚህ፡የመንግሥተ፡ሰማያት፡ደቀ፡መዝሙር፡የኾነ፡ጻፊ፡ዅሉ፡ከመዝገቡ፡ዐዲሱንና፡ አሮጌውን፡የሚያወጣ፡ባለቤትን፡ይመስላል፡አላቸው። 53፤ኢየሱስም፡እነዚህም፡ምሳሌዎች፡ከጨረሰ፡በዃላ፡ከዚያ፡ኼደ። 54፤ወደገዛ፡አገሩም፡መጥቶ፡እስኪገረሙ፡ድረስ፡በምኵራባቸው፡ያስተምራቸው፡ነበር፤እንዲህም፡ አሉ፦ይህን፡ጥበብና፡ተኣምራት፡ይህ፡ከወዴት፡አገኘው፧ 55፤ይህ፡የጸራቢ፡ልጅ፡አይደለምን፧እናቱስ፡ማርያም፡ትባል፡የለምን፧ወንድሞቹስ፡ያዕቆብና፡ዮሳ፡ስምዖንም፡ ይሁዳም፡አይደሉምን፧ 56፤እኅቶቹስ፡ዅሉ፡በእኛ፡ዘንድ፡ያሉ፡አይደሉምን፧እንኪያስ፡ይህን፡ዅሉ፡ከወዴት፡ አገኘው፧ተሰናከሉበትም። 57፤ኢየሱስ፡ግን፦ነቢይ፡ከገዛ፡አገሩና፡ከገዛ፡ቤቱ፡በቀር፡ሳይከበር፡አይቀርም፡አላቸው። 58፤ባለማመናቸውም፡ምክንያት፡በዚያ፡ብዙ፡ተኣምራት፡አላደረገም።

ምዕራፍ ፲፬

1፤በዚያ፡ዘመን፡የአራተኛው፡ክፍል፡ገዢ፡ሄሮድስ፡የኢየሱስን፡ዝና፡ሰማ፥ 2፤ለሎሌዎቹም፦ይህ፡መጥምቁ፡ዮሐንስ፡ነው፤ርሱ፡ከሙታን፡ተነሥቷል፥ስለዚህም፡ኀይል፡በርሱ፡ ይደረጋል፡አለ። 3፤ሄሮድስ፡በወንድሙ፡በፊልጶስ፡ሚስት፡በሄሮድያዳ፡ምክንያት፡ዮሐንስን፡አስይዞ፡አሳስሮት፡በወህኒ፡አኑሮት፡ ነበርና፤ 4፤ዮሐንስ፦ርሷ፡ለአንተ፡ትኾን፡ዘንድ፡አልተፈቀደም፡ይለው፡ነበርና። 5፤ሊገድለውም፡ወዶ፡ሳለ፥ሕዝቡ፡እንደ፡ነቢይ፡ስላዩት፡ፈራቸው። 6፤ነገር፡ግን፥ሄሮድስ፡የተወለደበት፡ቀን፡በኾነ፡ጊዜ፥የሄሮድያዳ፡ልጅ፡በመካከላቸው፡ዘፈነች፡ሄሮድስንም፡ ደስ፡አሠኘችው፤ 7፤ስለዚህም፡የምትለምነውን፡ዅሉ፡እንዲሰጣት፡በመሐላ፡ተስፋ፡አደረገላት። 8፤ርሷም፡በእናቷ፡ተመክራ፦የመጥምቁን፡የዮሐንስን፡ራስ፡በዚህ፡በወጭት፡ስጠኝ፡አለችው። 9፤ንጉሡም፡ዐዘነ፥ነገር፡ግን፥ስለ፡መሐላው፡ከርሱም፡ጋራ፡ተቀምጠው፡ስላሉት፡ሰዎች፡እንዲሰጧት፡ አዘዘ፤ 10፤ልኮም፡የዮሐንስን፡ራስ፡በወህኒ፡አስቈረጠው። 11፤ራሱንም፡በወጭት፡አምጥተው፡ለብላቴናዪቱ፡ሰጧት፥ወደ፡እናቷም፡ወሰደችው። 12፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ቀርበው፡በድኑን፡ወሰዱና፡ቀበሩት፥መጥተውም፡ለኢየሱስ፡አወሩለት። 13፤ኢየሱስም፡በሰማ፡ጊዜ፡ከዚያ፡ብቻውን፡ወደ፡ምድረ፡በዳ፡በታንኳ፡ፈቀቅ፡አለ፤ሕዝቡም፡ሰምተው፡ ከከተማዎቹ፡በእግር፡ተከተሉት። 14፤ወጥቶም፡ብዙ፡ሕዝብ፡አየና፡ዐዘነላቸው፡ድውዮቻቸውንም፡ፈወሰ። 15፤በመሸም፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ወደ፡ርሱ፡ቀርበው፦ቦታው፡ምድረ፡በዳ፡ነው፥አኹንም፡ሰዓቱ፡ ዐልፏል፤ወደ፡መንደሮች፡ኼደው፡ለራሳቸው፡ምግብ፡እንዲገዙ፡ሕዝቡን፡አሰናብት፡አሉት። 16፤ኢየሱስም፦እናንተ፡የሚበሉትን፡ስጧቸው፡እንጂ፡ሊኼዱ፡አያስፈልግም፡አላቸው። 17፤እነርሱም፦ከዐምስት፡እንጀራና፡ከኹለት፡ዓሣ፡በቀር፡በዚህ፡የለንም፡አሉት። 18፤ርሱም፦እነዚያን፡ወደዚህ፡አምጡልኝ፡አላቸው። 19፤ሕዝቡም፡በሣር፡ላይ፡እንዲቀመጡ፡አዘዘ፥ዐምስቱንም፡እንጀራና፡ኹለቱን፡ዓሣ፡ይዞ፡ወደ፡ሰማይ፡ አሻቅቦ፡አየና፡ባረከ፥እንጀራውንም፡ቈርሶ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ሰጠ፥ደቀ፡መዛሙርቱም፡ለሕዝቡ። 20፤ዅሉም፡በልተው፡ጠገቡ፥የተረፈውንም፡ቍርስራሽ፡ዐሥራ፡ኹለት፡መሶብ፡ሙሉ፡አነሡ። 21፤ከሴቶችና፡ከልጆችም፡በቀር፡የበሉት፡ዐምስት፡ሺሕ፡ወንዶች፡ያኽሉ፡ነበር። 22፤ወዲያውም፡ሕዝቡን፡ሲያሰናብት፡ሳለ፥ደቀ፡መዛሙርቱ፡በታንኳዪቱ፡ገብተው፡ወደ፡ማዶ፡ እንዲቀድሙት፡ግድ፡አላቸው። 23፤ሕዝቡንም፡አሰናብቶ፡ይጸልይ፡ዘንድ፡ብቻውን፡ወደ፡ተራራ፡ወጣ።በመሸም፡ጊዜ፡ብቻውን፡በዚያ፡ ነበረ። 24፤ታንኳዪቱም፡አኹን፡በባሕር፡መካከል፡ሳለች፥ነፋስ፡ከወደ፡ፊት፡ነበርና፥በማዕበል፡ትጨነቅ፡ነበር። 25፤ከሌሊቱም፡በአራተኛው፡ክፍል፡ኢየሱስ፡በባሕር፡ላይ፡እየኼደ፡ወደ፡እነርሱ፡መጣ። 26፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡በባሕር፡ላይ፡ሲኼድ፡ባዩት፡ጊዜ፦ምትሀት፡ነው፡ብለው፡ታወኩ፡በፍርሀትም፡ ጮኹ። 27፤ወዲያውም፡ኢየሱስ፡ተናገራቸውና፦አይዟችኹ፥እኔ፡ነኝ፤አትፍሩ፡አላቸው። 28፤ጴጥሮስም፡መልሶ፦ጌታ፡ሆይ፥አንተስ፡ከኾንኽ፡በውሃው፡ላይ፡ወዳንተ፡እንድመጣ፡እዘዘኝ፡አለው። 29፤ርሱም፦ና፡አለው።ጴጥሮስም፡ከታንኳዪቱ፡ወርዶ፡ወደ፡ኢየሱስ፡ሊደርስ፡በውሃው፡ላይ፡ኼደ። 30፤ነገር፡ግን፥የነፋሱን፡ኀይል፡አይቶ፡ፈራ፥ሊሰጥምም፡በዠመረ፡ጊዜ፦ጌታ፡ሆይ፥አድነኝ፡ብሎ፡ጮኸ። 31፤ወዲያውም፡ኢየሱስ፡እጁን፡ዘርግቶ፡ያዘውና፦አንተ፡እምነት፡የጐደለኽ፥ስለ፡ምን፡ ተጠራጠርኽ፧አለው። 32፤ወደ፡ታንኳዪቱም፡በወጡ፡ጊዜ፡ነፋሱ፡ተወ። 33፤በታንኳዪቱም፡የነበሩት፦በእውነት፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ነኽ፡ብለው፡ሰገዱለት። 34፤ተሻግረውም፡ወደ፡ጌንሴሬጥ፡ምድር፡መጡ። 35፤የዚያ፡ቦታ፡ሰዎችም፡ባወቁት፡ጊዜ፡በዙሪያው፡ወዳለ፡አገር፡ዅሉ፡ላኩ፥ሕመምተኛዎችንም፡ዅሉ፡ወደ፡ ርሱ፡አመጡ፤ 36፤የልብሱንም፡ጫፍ፡ብቻ፡ሊዳስሱ፡ይለምኑት፡ነበር፤የዳሰሱትም፡ዅሉ፡ዳኑ።

ምዕራፍ ፲፭

1፤በዚያን፡ጊዜ፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፡ከኢየሩሳሌም፡ወደ፡ኢየሱስ፡ቀረቡና፦ 2፤ደቀ፡መዛሙርትኽ፡ስለ፡ምን፡የሽማግሌዎችን፡ወግ፡ይተላለፋሉ፧እንጀራ፡ሲበሉ፡እጃቸውን፡ አይታጠቡምና፡አሉት። 3፤ርሱም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦እናንተስ፡ስለ፡ወጋችኹ፡የእግዚአብሔርን፡ትእዛዝ፡ስለ፡ምን፡ ትተላለፋላችኹ፧ 4፤እግዚአብሔር፦አባትኽንና፡እናትኽን፡አክብር፤ደግሞ፦አባቱን፡ወይም፡እናቱን፡የሰደበ፡ፈጽሞ፡ይሙት፡ ብሏልና፤ 5፤እናንተ፡ግን፦አባቱን፡ወይም፡እናቱን፦ከእኔ፡የምትጠቀምበት፡መባ፡ነው፡የሚል፡ዅሉ፥ 6፤አባቱን፡ወይም፡እናቱን፡አያከብርም፡ትላላችኹ፤ስለ፡ወጋችኹም፡የእግዚአብሔርን፡ቃል፡ሻራችኹ። 7፤እናንተ፡ግብዞች፥ኢሳይያስ፡ስለ፡እናንተ፦ 8፤ይህ፡ሕዝብ፡በከንፈሩ፡ያከብረኛል፥ልቡ፡ግን፡ከእኔ፡በጣም፡የራቀ፡ነው፤ 9፤የሰውም፡ሥርዐት፡የኾነ፡ትምህርት፡እያስተማሩ፡በከንቱ፡ያመልኩኛል፡ብሎ፡በእውነት፡ትንቢት፡ተናገረ። 10፤ሕዝቡንም፡ጠርቶ፦ስሙ፡አስተውሉም፤ 11፤ሰውን፡የሚያረክሰው፡ወደ፡አፍ፡የሚገባ፡አይደለም፥ከአፍ፡የሚወጣው፡ግን፡ሰውን፡የሚያረክሰው፡ይህ፡ ነው፡አላቸው። 12፤በዚያን፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ቀርበው፦ፈሪሳውያን፡ይህን፡ቃል፡ሰምተው፡እንደ፡ተሰናከሉ፡ ዐወቅኽን፧አሉት። 13፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፦የሰማዩ፡አባቴ፡ያልተከለው፡ተክል፡ዅሉ፡ይነቀላል። 14፤ተዉአቸው፤ዕውሮችን፡የሚመሩ፡ዕውሮች፡ናቸው፤ዕውርም፡ዕውርን፡ቢመራው፡ኹለቱም፡ወደ፡ ጕድጓድ፡ይወድቃሉ፡አለ። 15፤ጴጥሮስም፡መልሶ፦ምሳሌውን፡ተርጕምልን፡አለው። 16፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አለ፦እናንተ፡ደግሞ፡እስካኹን፡የማታስተውሉ፡ናችኹን፧ 17፤ወደ፡አፍ፡የሚገባ፡ዅሉ፡ወደ፡ሆድ፡ዐልፎ፡ወደ፡እዳሪ፡እንዲጣል፡አትመለከቱምን፧ 18፤ከአፍ፡የሚወጣ፡ግን፡ከልብ፡ይወጣል፥ሰውንም፡የሚያረክሰው፡ያ፡ነው። 19፤ከልብ፡ክፉ፡ዐሳብ፥መግደል፥ምንዝርነት፥ዝሙት፥መስረቅ፥በውሸት፡መመስከር፥ስድብ፡ይወጣልና። 20፤ሰውን፡የሚያረክሰው፡ይህ፡ነው፡እንጂ፥ባልታጠበ፡እጅ፡መብላትስ፡ሰውን፡አያረክሰውም። 21፤ኢየሱስም፡ከዚያ፡ወጥቶ፡ወደ፡ጢሮስና፡ወደ፡ሲዶና፡አገር፡ኼደ። 22፤እንሆም፥ከነናዊት276፡ሴት፡ከዚያ፡አገር፡ወጥታ፦ጌታ፡ሆይ፥የዳዊት፡ልጅ፥ማረኝ፤ልጄን፡ጋኔን፡ ክፉኛ፡ይዟታል፡ብላ፡ጮኸች። 23፤ርሱ፡ግን፡አንዳች፡አልመለሰላትም።ደቀ፡መዛሙርቱም፡ቀርበው፦በዃላችን፡ትጮኻለችና፡አሰናብታት፡ እያሉ፡ለመኑት። 24፤ርሱም፡መልሶ፦ከእስራኤል፡ቤት፡ለጠፉት፡በጎች፡በቀር፡አልተላክኹም፡አለ። 25፤ርሷ፡ግን፡መጥታ፦ጌታ፡ሆይ፥ርዳኝ፡እያለች፡ሰገደችለት። 26፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፦የልጆችን፡እንጀራ፡ይዞ፡ለቡችሎች፡መጣል፡አይገ፟ባ፟ም፡አለ። 27፤ርሷም፦አዎን፡ጌታ፡ሆይ፤ቡችሎችም፡እኮ፡ከጌታዎቻቸው፡ማእድ፡የወደቀውን፡ፍርፋሪ፡ይበላሉ፡ አለች። 28፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡መልሶ፦አንቺ፡ሴት፥እምነትሽ፡ታላቅ፡ነው፤እንደ፡ወደድሽ፡ይኹንልሽ፡ አላት።ልጇም፡ከዚያች፡ሰዓት፡ዠምሮ፡ዳነች። 29፤ኢየሱስም፡ከዚያ፡ዐልፎ፡ወደገሊላ፡ባሕር፡አጠገብ፡መጣ፥ወደ፡ተራራም፡ወጥቶ፡በዚያ፡ተቀመጠ። 30፤ብዙ፡ሕዝብም፡ዐንካሳዎችን፥ዕውሮችንም፥ዲዳዎችንም፥ጕንድሾችንም፥ሌላዎችንም፡ብዙ፡ይዘው፡ወደ፡ ርሱ፡ቀረቡ፥በኢየሱስም፡እግር፡አጠገብ፡ጣሏቸው፤ፈወሳቸውም፤ 31፤ስለዚህም፡ሕዝቡ፡ዲዳዎች፡ሲናገሩ፥ጕንድሾችም፡ሲድኑ፥ዐንካሳዎችም፡ሲኼዱ፥ዕውሮችም፡ሲያዩ፡ አይተው፡ተደነቁ፤የእስራኤልንም፡አምላክ፡አከበሩ። 32፤ኢየሱስም፡ደቀ፡መዛሙርቱን፡ጠርቶ፦ሕዝቡ፡ከእኔ፡ጋራ፡እስካኹን፡ሦስት፡ቀን፡ውለዋልና፥የሚበሉት፡ 276 ከነዓናዊት።ስለሌላቸው፡አዝንላቸዋለኹ፤በመንገድም፡እንዳይዝሉ፡ጦማቸውን፡ላሰናብታቸው፡አልወድም፡አላቸው። 33፤ደቀ፡መዛሙርቱም፦ይህን፡ያኽል፡ሕዝብ፡የሚያጠግብ፡ይህን፡ያኽል፡እንጀራ፡በምድረ፡በዳ፡ከወዴት፡ እናገኛለን፧አሉት። 34፤ኢየሱስም፦ስንት፡እንጀራ፡አላችኹ፧አላቸው።እነርሱም፦ሰባት፥ጥቂትም፡ትንሽ፡ዓሣ፡አሉት። 35፤ሕዝቡም፡በምድር፡ላይ፡እንዲቀመጡ፡አዘዘ፤ 36፤ሰባቱንም፡እንጀራ፡ዓሣውንም፡ይዞ፡አመሰገነ፡ቈርሶም፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ሰጠ፥ደቀ፡መዛሙርቱም፡ ለሕዝቡ። 37፤ዅሉም፡በሉና፡ጠገቡ፥የተረፈውንም፡ቍርስራሽ፡ሰባት፡ቅርጫት፡ሙሉ፡አነሡ። 38፤የበሉትም፡ከሴቶችና፡ከልጆች፡በቀር፡አራት፡ሺሕ፡ወንዶች፡ነበሩ። 39፤ሕዝቡንም፡ካሰናበተ፡በዃላ፡ወደ፡ታንኳዪቱ፡ገብቶ፡ወደመጌዶል፡አገር፡መጣ።

ምዕራፍ ፲፮

1፤ፈሪሳውያንና፡ሰዱቃውያንም፡ቀርበው፡ሲፈትኑት፡ከሰማይ፡ምልክት፡እንዲያሳያቸው፡ለመኑት። 2፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦በመሸ፡ጊዜ፦ሰማዩ፡ቀልቷልና፥ብራ፡ይኾናል፡ትላላችኹ፤ 3፤ማለዳም፦ሰማዩ፡ደምኖ፡ቀልቷልና፥ዛሬ፡ይዘንባል፡ትላላችኹ።የሰማዩን፡ፊትማ፡መለየት፡ ታውቃላችኹ፥የዘመኑንስ፡ምልክት፡መለየት፡አትችሉምን፧ 4፤ክፉና፡አመንዝራ፡ትውልድ፡ምልክት፡ይሻል፥ከነቢዩም፡ከዮናስ፡ምልክት፡በቀር፡ምልክት፡ አይሰጠውም።ትቷቸውም፡ኼደ። 5፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ወደ፡ማዶ፡በመጡ፡ጊዜ፡እንጀራ፡መያዝን፡ረሱ። 6፤ኢየሱስም፦ከፈሪሳውያንና፡ከሰዱቃውያን፡ርሾ፡ተጠንቀቁና፡ተጠበቁ፡አላቸው። 7፤እነርሱም፦እንጀራ፡ባንይዝ፡ነው፡ብለው፡ርስ፡በርሳቸው፡ተነጋገሩ። 8፤ኢየሱስም፡ዐውቆ፡እንዲህ፡አላቸው፦እናንተ፡እምነት፡የጐደላችኹ፥እንጀራ፡ስለሌላችኹ፡ስለ፡ምን፡ርስ፡ በርሳችኹ፡ትነጋገራላችኹ፧ገና፡አታስተውሉምን፧ 9፤ለዐምስቱ፡ሺሕ፡ዐምስቱ፡እንጀራ፥ስንት፡መሶብም፡እንዳነሣችኹ፡ትዝ፡አይላችኹምን፧ 10፤ወይስ፡ለአራቱ፡ሺሕ፡ሰባቱ፡እንጀራ፥ስንት፡ቅርጫትም፡እንዳነሣችኹ፡ትዝ፡አይላችኹምን፧ 11፤ከፈሪሳውያንና፡ከሰዱቃውያን፡ርሾ፡እንድትጠበቁ፡ብዬ፡ስለ፡እንጀራ፡እንዳልተናገርዃችኹ፡እንዴት፡ አታስተውሉምን፧ 12፤እነርሱም፡ከፈሪሳውያንና፡ከሰዱቃውያን፡ትምህርት፡እንጂ፡ከእንጀራ፡ርሾ፡እንዲጠበቁ፡እንዳላላቸው፡ያን፡ ጊዜ፡አስተዋሉ። 13፤ኢየሱስም፡ወደፊልጶስ፡ቂሳርያ፡አገር፡በደረሰ፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱን፦ሰዎች፡የሰውን፡ልጅ፡ማን፡ እንደ፡ኾነ፡ይሉታል፧ብሎ፡ጠየቀ። 14፤እነርሱም፦አንዳንዱ፡መጥምቁ፡ዮሐንስ፥ሌላዎችም፡ኤልያስ፥ሌላዎችም፡ኤርምያስ፡ወይም፡ከነቢያት፡ አንዱ፡ነው፡ይላሉ፡አሉት። 15፤ርሱም፦እናንተስ፡እኔን፡ማን፡እንደ፡ኾንኹ፡ትላላችኹ፧አላቸው። 16፤ስምዖን፡ጴጥሮስም፡መልሶ፦አንተ፡ክርስቶስ፡የሕያው፡እግዚአብሔር፡ልጅ፡ነኽ፡አለ። 17፤ኢየሱስም፡መልሶ፡እንዲህ፡አለው፦የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ሆይ፥በሰማያት፡ያለው፡አባቴ፡እንጂ፡ሥጋና፡ ደም፡ይህን፡አልገለጠልኽምና፡ብፁዕ፡ነኽ። 18፤እኔም፡እልኻለኹ፥አንተ፡ጴጥሮስ፡ነኽ፥በዚችም፡አለት፡ላይ፡ቤተ፡ክርስቲያኔን፡እሠራለኹ፥የገሃነም፡ ደጆችም፡አይችሏትም። 19፤የመንግሥተ፡ሰማያትንም፡መክፈቻዎች፡እሰጥኻለኹ፤በምድር፡የምታስረው፡ዅሉ፡በሰማያት፡የታሰረ፡ ይኾናል፥በምድርም፡የምትፈታው፡ዅሉ፡በሰማያት፡የተፈታ፡ይኾናል። 20፤ያን፡ጊዜም፡ርሱ፡ክርስቶስ፡እንደ፡ኾነ፡ለማንም፡እንዳይነግሩ፡ደቀ፡መዛሙርቱን፡አዘዛቸው። 21፤ከዚያን፡ቀን፡ዠምሮ፡ኢየሱስ፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ይኼድ፡ዘንድ፡ከሽማግሌዎችና፡ከካህናት፡አለቃዎች፡ ከጻፊዎችም፡ብዙ፡መከራ፡ይቀበልና፡ይገደል፡ዘንድ፡በሦስተኛውም፡ቀን፡ይነሣ፡ዘንድ፡እንዲገባው፡ለደቀ፡ መዛሙርቱ፡ይገልጥላቸው፡ዠመር። 22፤ጴጥሮስም፡ወደ፡ርሱ፡ወስዶ፦አይኹንብኽ፡ጌታ፡ሆይ፤ይህ፡ከቶ፡አይደርስብኽም፡ብሎ፡ሊገሥጸው፡ ዠመረ። 23፤ርሱ፡ግን፡ዘወር፡ብሎ፡ጴጥሮስን፦ወደ፡ዃላዬ፡ኺድ፥አንተ፡ሰይጣን፤የሰውን፡እንጂ፡ የእግዚአብሔርን፡አታስብምና፡ዕንቅፋት፡ኾነኽብኛል፡አለው። 24፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡እንዲህ፡አለ፦እኔን፡መከተል፡የሚወድ፡ቢኖር፥ራሱን፡ ይካድ፡መስቀሉንም፡ተሸክሞ፡ይከተለኝ። 25፤ነፍሱን፡ሊያድን፡የሚወድ፡ዅሉ፡ያጠፋታል፤ስለ፡እኔ፡ግን፡ነፍሱን፡የሚያጠፋ፡ዅሉ፡ያገኛታል። 26፤ሰው፡ዓለሙን፡ዅሉ፡ቢያተርፍ፡ነፍሱንም፡ቢያጐድል፡ምን፡ይጠቅመዋል፧ወይስ፡ሰው፡ስለ፡ነፍሱ፡ ቤዛ፡ምን፡ይሰጣል፧ 27፤የሰው፡ልጅ፡ከመላእክቱ፡ጋራ፡በአባቱ፡ክብር፡ይመጣ፡ዘንድ፡አለውና፤ያን፡ጊዜም፡ለዅሉ፡እንደ፡ሥራው፡ያስረክበዋል። 28፤እውነት፡እላችዃለኹ፥የሰው፡ልጅ፡በመንግሥቱ፡ሲመጣ፡እስኪያዩ፡ድረስ፡እዚህ፡ከሚቆሙት፡ሞትን፡ የማይቀምሱ፡አንዳንድ፡አሉ።

ምዕራፍ ፲፯

1፤ከስድስት፡ቀንም፡በዃላ፡ኢየሱስ፡ጴጥሮስንና፡ያዕቆብን፡ወንድሙንም፡ዮሐንስን፡ይዞ፡ወደ፡ረዥም፡ተራራ፡ ብቻቸውን፡አወጣቸው። 2፤በፊታቸውም፡ተለወጠ፥ፊቱም፡እንደ፡ፀሓይ፡በራ፥ልብሱም፡እንደ፡ብርሃን፡ነጭ፡ኾነ። 3፤እንሆም፥ሙሴና፡ኤልያስ፡ከርሱ፡ጋራ፡ሲነጋገሩ፡ታዩዋቸው። 4፤ጴጥሮስም፡መልሶ፡ኢየሱስን፦ጌታ፡ሆይ፥በዚህ፡መኾን፡ለእኛ፡መልካም፡ነው፤ብትወድስ፥በዚህ፡ ሦስት፡ዳስ፡አንዱን፡ለአንተ፡አንዱንም፡ለሙሴ፡አንዱንም፡ለኤልያስ፡እንሥራ፡አለ። 5፤ርሱም፡ገና፡ሲናገር፥እንሆ፥ብሩህ፡ደመና፡ጋረዳቸው፥እንሆም፥ከደመናው፦በርሱ፡ደስ፡የሚለኝ፡ የምወደ፟ው፡ልጄ፡ይህ፡ነው፤ርሱን፡ስሙት፡የሚል፡ድምፅ፡መጣ። 6፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ሰምተው፡በፊታቸው፡ወደቁ፡እጅግም፡ፈርተው፡ነበር። 7፤ኢየሱስም፡ቀርቦ፡ዳሰሳቸውና፦ተነሡ፡አትፍሩም፡አላቸው። 8፤ዐይናቸውንም፡አቅንተው፡ሲያዩ፡ከኢየሱስ፡ብቻ፡በቀር፡ማንንም፡አላዩም። 9፤ከተራራውም፡በወረዱ፡ጊዜ፥ኢየሱስ፦የሰው፡ልጅ፡ከሙታን፡እስኪነሣ፡ድረስ፡ያያችኹትን፡ለማንም፡አትንገሩ፡ብሎ፡አዘዛቸው። 10፤ደቀ፡መዛሙርቱም፦እንግዲህ፡ጻፊዎች፦ኤልያስ፡አስቀድሞ፡ሊመጣ፡ይገ፟ባ፟ዋል፡ስለ፡ምን፡ ይላሉ፧ብለው፡ጠየቁት። 11፤ኢየሱስም፡መልሶ፦ኤልያስማ፡አስቀድሞ፡ይመጣል፡ዅሉንም፡ያቀናል፤ 12፤ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥ኤልያስ፡ከዚህ፡በፊት፡መጣ፤የወደዱትንም፡ዅሉ፡አደረጉበት፡እንጂ፡ አላወቁትም፤እንዲሁም፡ደግሞ፡የሰው፡ልጅ፡ከነርሱ፡መከራ፡ይቀበል፡ዘንድ፡አለው፡አላቸው። 13፤በዚያን፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ስለ፡መጥምቁ፡ስለ፡ዮሐንስ፡እንደ፡ነገራቸው፡አስተዋሉ። 14፤ወደ፡ሕዝቡም፡ሲደርሱ፡አንድ፡ሰው፡ወደ፡ርሱ፡ቀረበና፡ተንበርክኮ፦ጌታ፡ሆይ፥ልጄን፡ ማርልኝ፥በጨረቃ፡እየተነሣበት፡ክፉኛ፡ይሣቀያልና፤ 15፤ብዙ፡ጊዜ፡በእሳት፡ብዙ፡ጊዜም፡በውሃ፡ይወድቃልና። 16፤ወደ፡ደቀ፡መዛሙርትኽም፡አመጣኹት፡ሊፈውሱትም፡አቃታቸው፡አለው። 17፤ኢየሱስም፡መልሶ፦የማታምን፡ጠማማ፡ትውልድ፡ሆይ፥እስከ፡መቼ፡ከእናንተ፡ጋራ፡እኖራለኹ፧እስከ፡ መቼስ፡እታገሣችዃለኹ፧ወደዚህ፡ወደ፡እኔ፡አምጡት፡አለ። 18፤ኢየሱስም፡ገሠጸው፡ጋኔኑም፡ከርሱ፡ወጣ፥ብላቴናውም፡ከዚያች፡ሰዓት፡ዠምሮ፡ተፈወሰ። 19፤ከዚህ፡በዃላ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ብቻቸውን፡ወደ፡ኢየሱስ፡ቀረቡና፦እኛ፡ልናወጣው፡ያልቻልን፡ስለ፡ ምን፡ነው፧አሉት። 20፤ኢየሱስም፦ስለእምነታችኹ፡ማነስ፡ነው፤እውነት፡እላችዃለኹ፥የሰናፍጭ፡ቅንጣት፡የሚያኽል፡እምነት፡ ቢኖራችኹ፥ይህን፡ተራራ፦ከዚህ፡ወደዚያ፡ዕለፍ፡ብትሉት፡ያልፋል፤የሚሳናችኹም፡ነገር፡የለም። 21፤ይህ፡ዐይነት፡ግን፡ከጸሎትና፡ከጦም፡በቀር፡አይወጣም፡አላቸው። 22፤በገሊላም፡ሲመላለሱ፥ኢየሱስ፦የሰው፡ልጅ፡በሰዎች፡እጅ፡ዐልፎ፡ይሰጥ፡ዘንድ፡ አለው፥ይገድሉትማል፥ 23፤በሦስተኛውም፡ቀን፡ይነሣል፡አላቸው።እጅግም፡ዐዘኑ። 24፤ወደ፡ቅፍርናሖምም፡በመጡ፡ጊዜ፡ግብር፡የሚቀበሉ፡ሰዎች፡ወደ፡ጴጥሮስ፡ቀረቡና፦መምህራችኹ፡ ኹለቱን፡ዲናር፡አይገብርምን፧አሉት። 25፤አዎን፡ይገብራል፡አለ።ወደ፡ቤትም፡በገባ፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡አስቀድሞ፦ስምዖን፡ሆይ፥ምን፡ ይመስልኻል፧የምድር፡ነገሥታት፡ቀረጥና፡ግብር፡ከማን፡ይቀበላሉ፧ከልጆቻቸውን፡ወይስ፡ ከእንግዳዎች፧አለው። 26፤ጴጥሮስም፦ከእንግዳዎች፡ባለው፡ጊዜ፡ኢየሱስ፦እንኪያስ፡ልጆቻቸው፡ነጻ፡ናቸው። 27፤ነገር፡ግን፥እንዳናሰናክላቸው፥ወደ፡ባሕር፡ኺድና፡መቃጥን፡ጣል፥መዠመሪያም፡የሚወጣውን፡ዓሣ፡ ውሰድና፡አፉን፡ስትከፍት፡ስታቴር፡ታገኛለኽ፤ያን፡ወስደኽ፡ስለ፡እኔና፡ስለ፡አንተ፡ስጣቸው፡አለው።

  • ፤አንድ፡ዲናር፡ዐምሳ፡የኢትዮጵያ፡ብር፡ሳንቲም፡ያኽል፡ነው።
    • ፤ስታቴር፡ኹለት፡ብር፡ያኽል፡ነው።

ምዕራፍ ፲፰

1፤በዚያች፡ሰዓት፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ወደ፡ኢየሱስ፡ቀርበው፦በመንግሥተ፡ሰማያት፡ከዅሉ፡የሚበልጥ፡ማን፡ ይኾን፧አሉት። 2፤ሕፃንም፡ጠርቶ፡በመካከላቸው፡አቆመ፡ 3፤እንዲህም፡አለ፦እውነት፡እላችዃለኹ፥ካልተመለሳችኹ፡እንደ፡ሕፃናትም፡ካልኾናችኹ፥ወደ፡መንግሥተ፡ ሰማያት፡ከቶ፡አትገቡም። 4፤እንግዲህ፡እንደዚህ፡ሕፃን፡ራሱን፡የሚያዋርድ፡ዅሉ፥በመንግሥተ፡ሰማያት፡የሚበልጥ፡ርሱ፡ነው። 5፤እንደዚህም፡ያለውን፡አንድ፡ሕፃን፡በስሜ፡የሚቀበል፡ዅሉ፡እኔን፡ይቀበላል፤ 6፤በእኔም፡ከሚያምኑ፡ከነዚህ፡ከታናናሾቹ፡አንዱን፡የሚያሰናክል፡ዅሉ፥የወፍጮ፡ድንጋይ፡በዐንገቱ፡ታስሮ፡ ወደ፡ጥልቅ፡ባሕር፡መስጠም፡ይሻለው፡ነበር። 7፤ወዮ፡ለዓለም፡ስለ፡ማሰናከያ፤ማሰናከያ፡ሳይመጣ፡አይቀርምና፥ነገር፡ግን፥በርሱ፡ጠንቅ፡ማሰናከያ፡ ለሚመጣበት፡ለዚያ፡ሰው፡ወዮለት። 8፤እጅኽ፡ወይም፡እግርኽ፡ብታሰናክልኽ፥ቈርጠኽ፡ከአንተ፡ጣላት፤ኹለት፡እጅ፡ወይም፡ኹለት፡እግር፡ ኖሮኽ፡ወደዘለዓለም፡እሳት፡ከምትጣል፡ይልቅ፡ዐንካሳ፡ወይም፡ጕንድሽ፡ኾነኽ፡ወደ፡ሕይወት፡መግባት፡ ይሻልኻል። 9፤ዐይንኽ፡ብታሰናክልኽ፡አውጥተኽ፡ከአንተ፡ጣላት፤ኹለት፡ዐይን፡ኖሮኽ፡ወደ፡ገሃነመ፡እሳት፡ከምትጣል፡ ይልቅ፡አንዲት፡ዐይን፡ኖራኽ፡ወደ፡ሕይወት፡መግባት፡ይሻልኻል። 10፤ከነዚህ፡ከታናናሾቹ፡አንዱን፡እንዳትንቁ፡ተጠንቀቁ፤መላእክታቸው፡በሰማያት፡ዘወትር፡በሰማያት፡ያለውን፡ የአባቴን፡ፊት፡ያያሉ፡እላችዃለኹና። 11፤የሰው፡ልጅ፡የጠፋውን፡ለማዳን፡መጥቷልና። 12፤ምን፡ይመስላችዃል፧ላንድ፡ሰው፡መቶ፡በጎች፡ቢኖሩት፡ከነርሱም፡አንዱ፡ቢባዝን፥ዘጠና፡ዘጠኙን፡ በተራራ፡ትቶ፡ኼዶም፡የባዘነውን፡አይፈልግምን፧ 13፤ቢያገኘውም፥እውነት፡እላችዃለኹ፥ካልባዘኑቱ፡ከዘጠና፡ዘጠኙ፡ይልቅ፡በርሱ፡ደስ፡ይለዋል። 14፤እንደዚሁ፡ከነዚህ፡ከታናናሾቹ፡አንዱ፡እንዲጠፋ፡በሰማያት፡ያለው፡አባታችኹ፡ፈቃድ፡አይደለም። 15፤ወንድምኽም፡ቢበድልኽ፥ኼደኽ፡አንተና፡ርሱ፡ብቻችኹን፡ኾናችኹ፡ውቀሰው።ቢሰማኽ፥ወንድምኽን፡ ገንዘብ፡አደረግኸው፤ 16፤ባይሰማኽ፡ግን፥በኹለት፡ወይም፡በሦስት፡ምስክር፡አፍ፡ነገር፡ዅሉ፡እንዲጸና፥ዳግመኛ፡አንድ፡ወይም፡ ኹለት፡ከአንተ፡ጋራ፡ውሰድ፤ 17፤እነርሱንም፡ባይሰማ፥ለቤተ፡ክርስቲያን፡ንገራት፤ደግሞም፡ቤተ፡ክርስቲያንን፡ባይሰማት፥እንደ፡አረመኔና፡ እንደ፡ቀራጭ፡ይኹንልኽ። 18፤እውነት፡እላችዃለኹ፥በምድር፡የምታስሩት፡ዅሉ፡በሰማይ፡የታሰረ፡ይኾናል፥በምድርም፡የምትፈቱት፡ ዅሉ፡በሰማይ፡የተፈታ፡ይኾናል። 19፤ደግሞ፡እላችዃለኹ፥ከእናንተ፡ኹለቱ፡በምድር፡በማናቸውም፡በሚለምኑት፡ነገር፡ዅሉ፡ቢስማሙ፡በሰማያት፡ካለው፡ከአባቴ፡ዘንድ፡ይደረግላቸዋል። 20፤ኹለት፡ወይም፡ሦስት፡በስሜ፡በሚሰበሰቡበት፡በዚያ፡በመካከላቸው፡እኾናለኹና። 21፤በዚያን፡ጊዜ፡ጴጥሮስ፡ወደ፡ርሱ፡ቀርቦ፦ጌታ፡ሆይ፥ወንድሜ፡ቢበድለኝ፡ስንት፡ጊዜ፡ልተውለት፧እስከ፡ሰባት፡ጊዜን፧አለው። 22፤ኢየሱስ፡እንዲህ፡አለው፦እስከ፡ሰባ፡ጊዜ፡ሰባት፡እንጂ፡እስከ፡ሰባት፡ጊዜ፡አልልኽም። 23፤ስለዚህ፥መንግሥተ፡ሰማያት፡ባሮቹን፡ሊቈጣጠር፡የወደደን፡ንጉሥ፡ትመስላለች። 24፤መቈጣጠርም፡በዠመረ፡ጊዜ፥እልፍ፡መክሊት፡ዕዳ፡ያለበትን፡አንድ፡ሰው፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ። 25፤የሚከፍለውም፡ቢያጣ፥ርሱና፡ሚስቱ፡ልጆቹም፡ያለውም፡ዅሉ፡እንዲሸጥና፡ዕዳው፡እንዲከፈል፡ጌታው፡አዘዘ። 26፤ስለዚህ፥ባሪያው፡ወድቆ፡ሰገደለትና፦ጌታ፡ሆይ፥ታገሠኝ፥ዅሉንም፡እከፍልኻለኹ፡አለው። 27፤የዚያም፡ባሪያ፡ጌታ፡ዐዘነለትና፡ለቀቀው፥ዕዳውንም፡ተወለት። 28፤ነገር፡ግን፥ያ፡ባሪያ፡ወጥቶ፡ከባልንጀራዎቹ፡ከባሮቹ፡መቶ፡ዲናር፡ዕዳ፡ያለበትን፡አንዱን፡ አገኘና፦ዕዳኽን፡ክፈለኝ፡ብሎ፡ያዘና፡ዐነቀው። 29፤ስለዚህ፥ባልንጀራው፡ባሪያ፡ወድቆ፦ታገሠኝ፥ዅሉንም፡እከፍልኻለኹ፡ብሎ፡ለመነው። 30፤ርሱም፡አልወደደም፥ግን፡ኼዶ፡ዕዳውን፡እስኪከፍል፡ድረስ፡በወህኒ፡አኖረው። 31፤ባልንጀራዎቹ፡የኾኑ፡ባሪያዎችም፡ያደረገውን፡አይተው፡እጅግ፡ዐዘኑ፥መጥተውም፡የኾነውን፡ዅሉ፡ ለጌታቸው፡ገለጡ። 32፤ከዚያ፡ወዲያ፡ጌታው፡ጠርቶ፦አንተ፡ክፉ፡ባሪያ፥ስለ፡ለመንኸኝ፡ያን፡ዕዳ፡ዅሉ፡ተውኹልኽ፤ 33፤እኔ፡እንደ፡ማርኹኽ፡ባልንጀራኽ፡የኾነውን፡ያን፡ባሪያ፡ልትምረው፡ለአንተስ፡አይገ፟ባ፟ኽምን፧አለው። 34፤ጌታውም፡ተቈጣና፡ዕዳውን፡ዅሉ፡እስኪከፍለው፡ድረስ፡ለሚሣቅዩት፡አሳልፎ፡ሰጠው። 35፤ከእናንተ፡እያንዳንዱ፡ወንድሙን፡ከልቡ፡ይቅር፡ካላለ፥እንዲሁ፡ደግሞ፡የሰማዩ፡አባቴ፡ያደርግባችዃል።

ምዕራፍ ፲፱

1፤ኢየሱስም፡ይህን፡ነገር፡ከፈጸመ፡በዃላ፥ከገሊላ፡ኼዶ፡ወደይሁዳ፡አውራጃ፡ወደዮርዳኖስ፡ማዶ፡መጣ። 2፤ብዙ፡ሕዝብም፡ተከተሉት፥በዚያም፡ፈወሳቸው። 3፤ፈሪሳውያንም፡ወደ፡ርሱ፡ቀረቡና፡ሲፈትኑት፦ሰው፡በኾነው፡ምክንያት፡ዅሉ፡ሚስቱን፡ሊፈታ፡ ተፈቅዶለታልን፧አሉት። 4፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፡እንዲህ፡አለ፦ፈጣሪ፡በመዠመሪያ፡ወንድና፡ሴት፡አደረጋቸው፥ 5፤አለም፦ስለዚህ፡ሰው፡አባቱንና፡እናቱን፡ይተዋል፥ከሚስቱም፡ጋራ፡ይተባበራል፥ኹለቱም፡አንድ፡ሥጋ፡ ይኾናሉ፡የሚለውን፡ቃል፡አላነበባችኹምን፧ 6፤ስለዚህ፥አንድ፡ሥጋ፡ናቸው፡እንጂ፡ወደ፡ፊት፡ኹለት፡አይደሉም።እግዚአብሔር፡ያጣመረውን፡ እንግዲህ፡ሰው፡አይለየው። 7፤እነርሱም፦እንኪያስ፡ሙሴ፡የፍቿን፡ጽሕፈት፡ሰጥተው፡እንዲፈቷት፡ስለ፡ምን፡አዘዘ፧አሉት። 8፤ርሱም፦ሙሴስ፡ስለልባችኹ፡ጥንካሬ፡ሚስቶቻችኹን፡ትፈቱ፡ዘንድ፡ፈቀደላችኹ፤ከጥንት፡ግን፡እንዲህ፡ አልነበረም። 9፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥ያለዝሙት፡ምክንያት፡ሚስቱን፡ፈቶ፟፡ሌላዪቱን፡የሚያገባ፡ዅሉ፡ ያመነዝራል፥የተፈታችውንም፡የሚያገባ፡ያመነዝራል፡አላቸው። 10፤ደቀ፡መዛሙርቱም፦የባልና፡የሚስት፡ሥርዐት፡እንዲህ፡ከኾነ፡መጋባት፡አይጠቅምም፡አሉት። 11፤ርሱ፡ግን፦ይህ፡ነገር፡ለተሰጣቸው፡ነው፡እንጂ፡ለዅሉ፡አይደለም፤ 12፤በእናት፡ማሕፀን፡ጃን፡ደረባዎች፡ኾነው፡የተወለዱ፡አሉ፥ሰውም፡የሰለባቸው፡ጃን፡ደረባዎች፡አሉ፥ስለ፡ መንግሥተ፡ሰማያትም፡ራሳቸውን፡የሰለቡ፡ጃን፡ደረባዎች፡አሉ፦ሊቀበለው፡የሚችል፡ይቀበለው፡አላቸው። 13፤በዚያን፡ጊዜ፡እጁን፡እንዲጭንባቸውና፡እንዲጸልይ፡ሕፃናትን፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ ገሠጿቸው። 14፤ነገር፡ግን፥ኢየሱስ፦ሕፃናትን፡ተዉአቸው፥ወደ፡እኔም፡ይመጡ፡ዘንድ፡አትከልክሏቸው፤መንግሥተ፡ ሰማያት፡እንደነዚህ፡ላሉ፡ናትና፥አለ፤ 15፤እጁንም፡ጫነባቸውና፡ከዚያ፡ኼደ። 16፤እንሆም፥አንድ፡ሰው፡ቀርቦ፦መምህር፡ሆይ፥የዘለዓለምን፡ሕይወት፡እንዳገኝ፡ምን፡መልካም፡ነገር፡ ላድርግ፧አለው። 17፤ርሱም፦ስለ፡መልካም፡ነገር፡ለምን፡ትጠይቀኛለኽ፧መልካም፡የኾነ፡አንድ፡ነው፤ወደ፡ሕይወት፡ መግባት፡ብትወድ፡ግን፡ትእዛዛትን፡ጠብቅ፡አለው። 18፤ርሱም፦የትኛዎችን፧አለው።ኢየሱስም፦አትግደል፥አታመንዝር፥አትስረቅ፥በሐሰት፡አትመስክር፥ 19፤አባትኽንና፡እናትኽን፡አክብር፥ባልንጀራኽንም፡እንደ፡ራስኽ፡ውደድ፡አለው። 20፤ጐበዙም፦ይህንማ፡ዅሉ፡ከሕፃንነቴ፡ዠምሬ፡ጠብቄያለኹ፥ደግሞስ፡የሚጐድለኝ፡ምንድር፡ ነው፧አለው። 21፤ኢየሱስም፦ፍጹም፡ልትኾን፡ብትወድ፥ኺድና፡ያለኽን፡ሸጠኽ፡ለድኻዎች፡ስጥ፥መዝገብም፡በሰማያት፡ ታገኛለኽ፥መጥተኽም፡ተከተለኝ፡አለው። 22፤ጐበዙም፡ይህን፡ቃል፡በሰማ፡ጊዜ፡ብዙ፡ንብረት፡ነበረውና፡እያዘነ፡ኼደ። 23፤ኢየሱስም፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፦እውነት፡እላችዃለኹ፥ለባለጠጋ፡ወደ፡መንግሥተ፡ሰማያት፡መግባት፡ ጭንቅ፡ነው። 24፤ዳግመኛም፡እላችዃለኹ፥ባለጠጋ፡ወደእግዚአብሔር፡መንግሥት፡ከሚገባ፡ግመል፡በመርፌ፡ቀዳዳ፡ቢገባ፡ይቀላል፡አለ። 25፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ሰምተው፡እጅግ፡ተገረሙና፦እንኪያስ፡ማን፡ሊድን፡ይችላል፧አሉ። 26፤ኢየሱስም፡እነርሱን፡ተመልክቶ፦ይህ፡በሰው፡ዘንድ፡አይቻልም፡በእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ግን፡ዅሉ፡ ይቻላል፡አላቸው። 27፤በዚያን፡ጊዜ፡ጴጥሮስ፡መልሶ፦እንሆ፥እኛ፡ዅሉን፡ትተን፡ተከተልንኽ፤እንኪያስ፡ምን፡እናገኝ፡ ይኾን፧አለው። 28፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አላቸው፦እውነት፡እላችዃለኹ፥እናንተስ፡የተከተላችኹኝ፥በዳግመኛ፡ልደት፡የሰው፡ልጅ፡በክብሩ፡ዙፋን፡በሚቀመጥበት፡ጊዜ፥እናንተ፡ደግሞ፡በዐሥራ፡ኹለቱ፡የእስራኤል፡ነገድ፡ ስትፈርዱ፡በዐሥራ፡ኹለት፡ዙፋን፡ትቀመጣላችኹ። 29፤ስለ፡ስሜም፡ቤቶችን፡ወይም፡ወንድሞችን፡ወይም፡እኅቶችን፡ወይም፡አባትን፡ወይም፡እናትን፡ወይም፡ ሚስትን፡ወይም፡ልጆችን፡ወይም፡ዕርሻን፡የተወ፡ዅሉ፡መቶ፡ዕጥፍ፡ይቀበላል፡የዘለዓለምንም፡ሕይወት፡ ይወርሳል። 30፤ነገር፡ግን፥ብዙዎቹ፡ፊተኛዎች፡ዃለኛዎች፥ዃለኛዎችም፡ፊተኛዎች፡ይኾናሉ።

ምዕራፍ ፳

1፤መንግሥተ፡ሰማያት፡ለወይኑ፡አትክልት፡ሠራተኛዎችን፡ሊቀጥር፡ማልዶ፡የወጣ፡ባለቤት፡ሰውን፡ ትመስላለችና። 2፤ሠራተኛዎችንም፡በቀን፡አንድ፡ዲናር፡ተስማምቶ፡ወደወይኑ፡አትክልት፡ሰደዳቸው። 3፤በሦስት፡ሰዓትም፡ወጥቶ፡ሥራ፡የፈቱ፡ሌላዎችን፡በአደባባይ፡ቆመው፡አየ፥ 4፤እነዚያንም፦እናንተ፡ደግሞ፡ወደወይኔ፡አትክልት፡ኺዱ፥የሚገ፟ባ፟ውንም፡እሰጣችዃለኹ፡አላቸው።እነርሱም፡ኼዱ። 5፤ደግሞም፡በስድስትና፡በዘጠኝ፡ሰዓት፡ወጥቶ፡እንዲሁ፡አደረገ። 6፤በዐሥራ፡አንደኛውም፡ሰዓት፡ወጥቶ፡ሌላዎችን፡ቆመው፡አገኘና፦ሥራ፡ፈታ፟ችኹ፡ቀኑን፡ዅሉ፡በዚህ፡ ስለ፡ምን፡ትቆማላችኹ፧አላቸው። 7፤የሚቀጥረን፡ስላጣን፡ነው፡አሉት።ርሱም፦እናንተ፡ደግሞ፡ወደወይኔ፡አትክልት፡ኺዱ፥የሚገ፟ባ፟ውንም፡ ትቀበላላችኹ፡አላቸው። 8፤በመሸም፡ጊዜ፡የወይኑ፡አትክልት፡ጌታ፡አዛዡን፦ሠራተኛዎችን፡ጥራና፡ከዃለኛዎች፡ዠምረኽ፡እስከ፡ ፊተኛዎች፡ድረስ፡ደመ፡ወዝ፡ስጣቸው፡አለው። 9፤በዐሥራ፡አንደኛው፡ሰዓትም፡የገቡ፡መጥተው፡እያንዳንዳቸው፡አንድ፡ዲናር፡ተቀበሉ። 10፤ፊተኛዎችም፡በመጡ፡ጊዜ፡አብዝተው፡የሚቀበሉ፡መስሏቸው፡ነበር፤እነርሱም፡ደግሞ፡እያንዳንዳቸው፡ አንድ፡ዲናር፡ተቀበሉ። 11-12፤ተቀብለውም፦እነዚህ፡ዃለኛዎች፡አንድ፡ሰዓት፡ሠሩ፥የቀኑንም፡ድካምና፡ትኵሳት፡ከተሸከምን፡ ከእኛ፡ጋራ፡አስተካከልኻቸው፡ብለው፡በባለቤቱ፡ላይ፡አንጐራጐሩ። 13፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፡ከነርሱ፡ለአንዱ፡እንዲህ፡አለው፦ወዳጄ፡ሆይ፥አልበ፡ደቀ፡መዛሙርት፡ብቻቸውን፡ ወደ፡ርሱ፡አቅርቦ። ደልኹኽም፡ባንድ፡ዲናር፡ አልተስማማኸኝምን፧ 14፤ድርሻኽን፡ውሰድና፡ኺድ፤እኔ፡ለዚህ፡ለዃለኛው፡እንደ፡አንተ፡ልሰጠው፡እወዳለኹ፤በገንዘቤ፡ የወደድኹትን፡ኣደርግ፡ዘንድ፡መብት፡የለኝምን፧ 15፤ወይስ፡እኔ፡መልካም፡ስለ፡ኾንኹ፡ዐይንኽ፡ምቀኛ፡ናትን፧ 16፤እንዲሁ፡ዃለኛዎች፡ፊተኛዎች፥ፊተኛዎችም፡ዃለኛዎች፡ይኾናሉ፤የተጠሩ፡ብዙዎች፥የተመረጡ፡ግን፡ ጥቂቶች፡ናቸውና። 17፤ኢየሱስም፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ሊወጣ፡ሳለ፥በመንገድ፡ዐሥራ፡ኹለቱን 18፤እንሆ፥ወደ፡ኢየሩሳሌም፡እንወጣለን፥የሰው፡ልጅም፡ለካህናት፡አለቃዎችና፡ለጻፊዎች፡ይሰጣል፤የሞት፡ ፍርድም፡ይፈርዱበታል፥ 19፤ሊዘባበቱበትም፡ሊገርፉትም፡ሊሰቅሉትም፡ለአሕዛብ፡አሳልፈው፡ይሰጡታል፥በሦስተኛውም፡ቀን፡ይነሣል፡ አላቸው። 20፤በዚያን፡ጊዜ፡የዘብዴዎስ፡ልጆች፡እናት፡ከልጆቿ፡ጋራ፡እየሰገደችና፡አንድ፡ነገር፡እየለመነች፡ወደ፡ ርሱ፡ቀረበች። 21፤ርሱም፦ምን፡ትፈልጊያለሽ፧አላት።ርሷም፦እነዚህ፡ኹለቱ፡ልጆቼ፡አንዱ፡በቀኝኽ፡አንዱም፡በግራኽ፡ በመንግሥትኽ፡እንዲቀመጡ፡እዘዝ፡አለችው። 22፤ኢየሱስ፡ግን፡መልሶ፦የምትለምኑትን፡አታውቁም፦እኔ፡ልጠጣው፡ያለውን፡ጽዋ፡ልትጠጡ፡እኔም፡ የምጠመቀውን፡ጥምቀት፡ልትጠመቁ፡ትችላላችኹን፧አለ።እንችላለን፡አሉት። 23፤ርሱም፦ጽዋዬንስ፡ትጠጣላችኹ፤በቀኝና፡በግራ፡መቀመጥ፡ግን፡ከአባቴ፡ዘንድ፡ለተዘጋጀላቸው፡ነው፡ እንጂ፡እኔ፡የምሰጥ፡አይደለኹም፡አላቸው። 24፤ዐሥሩም፡ሰምተው፡በኹለቱ፡ወንድማማች፡ተቈጡ። 25፤ኢየሱስ፡ግን፡ወደ፡ርሱ፡ጠርቶ፡እንዲህ፡አላቸው፦የአሕዛብ፡አለቃዎች፡እንዲገዟቸው፡ታላላቆቹም፡ በላያቸው፡እንዲሠለጥኑ፡ታውቃላችኹ። 26፤በእናንተስ፡እንዲህ፡አይደለም፤ነገር፡ግን፥ማንም፡ከእናንተ፡ታላቅ፡ሊኾን፡የሚወድ፡የእናንተ፡አገልጋይ፡ ይኹን፥ 27፤ከእናንተም፡ማንም፡ፊተኛ፡ሊኾን፡የሚወድ፡የእናንተ፡ባሪያ፡ይኹን፤ 28፤እንዲሁም፡የሰው፡ልጅ፡ሊያገለግል፡ነፍሱንም፡ለብዙዎች፡ቤዛ፡ሊሰጥ፡እንጂ፡እንዲያገለግሉት፡ አልመጣም። 29፤ከኢያሪኮም፡ሲወጡ፡ብዙ፡ሕዝብ፡ተከተሉት። 30፤እንሆም፥ኹለት፡ዕውሮች፡በመንገድ፡ዳር፡ተቀምጠው፥ኢየሱስ፡እንዲያልፍ፡በሰሙ፡ጊዜ፦ጌታ፡ ሆይ፥የዳዊት፡ልጅ፥ማረን፡ብለው፡ጮኹ። 31፤ሕዝቡም፡ዝም፡እንዲሉ፡ገሠጿቸው፤እነርሱ፡ግን፦ጌታ፡ሆይ፥የዳዊት፡ልጅ፥ማረን፡እያሉ፡ አብዝተው፡ጮኹ። 32፤ኢየሱስም፡ቆሞ፡ጠራቸውና፦ምን፡ላደርግላችኹ፡ትወዳላችኹ፧አለ። 33፤ጌታ፡ሆይ፥ዐይኖቻችን፡ይከፈቱ፡ዘንድ፡አሉት። 34፤ኢየሱስም፡ዐዘነላቸውና፡ዐይኖቻቸውን፡ዳሰሰ፥ወዲያውም፡አዩና፡ተከተሉት።

ምዕራፍ ፳፩

1፤ወደ፡ኢየሩሳሌምም፡ቀርበው፡ወደ፡ደብረ፡ዘይት፡ወደ፡ቤተ፡ፋጌ፡ሲደርሱ፥ያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡ከደቀ፡ መዛሙርቱ፡ኹለት፡ላከ፥ 2፤እንዲህም፡አላቸው፦በፊታችኹ፡ወዳለችው፡መንደር፡ኺዱ፥በዚያን፡ጊዜም፡የታሰረችን፡አህያ፡ ውርንጫም፡ከርሷ፡ጋራ፡ታገኛላችኹ፤ፈታ፟ችኹ፡አምጡልኝ። 3፤ማንም፡አንዳች፡ቢላችኹ፦ለጌታ፡ያስፈልጉታል፡በሉ፤ወዲያውም፡ይሰዳቸዋል። 4-5፤ለጽዮን፡ልጅ፦እንሆ፥ንጉሥሽ፡የዋህ፡ኾኖ፡በአህያ፡ላይና፡በአህያዪቱ፡ግልገል፡በውርንጫዪቱ፡ላይ፡ ተቀምጦ፡ወደ፡አንቺ፡ይመጣል፡በሏት፡ተብሎ፡በነቢይ፡የተነገረው፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ይህ፡ኾነ። 6፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ኼደው፡ኢየሱስ፡እንዳዘዛቸው፡አደረጉ፥ 7፤አህያዪቱንና፡ውርንጫዋንም፡አመጡለት፥ልብሳቸውንም፡በእነርሱ፡ላይ፡ጫኑ፥ተቀመጠባቸውም። 8፤ከሕዝቡም፡እጅግ፡ብዙዎች፡ልብሳቸውን፡በመንገድ፡ላይ፡አነጠፉ፥ሌላዎችም፡ከዛፍ፡ጫፍ፡ጫፉን፡ እየቈረጡ፡በመንገድ፡ላይ፡ያነጥፉ፡ነበር። 9፤የሚቀድሙትም፡ሕዝብ፡የሚከተሉትም፦ሆሣዕና፡ለዳዊት፡ልጅ፡በጌታ፡ስም፡የሚመጣ፡የተባረከ፡ ነው፤ሆሣዕና፡በአርያም፡እያሉ፡ይጮኹ፡ነበር። 10፤ወደ፡ኢየሩሳሌምም፡በገባ፡ጊዜ፡መላው፡ከተማ፦ይህ፡ማን፡ነው፧ብሎ፡ተናወጠ። 11፤ሕዝቡም፦ይህ፡ከገሊላ፡ናዝሬት፡የመጣ፡ነቢዩ፡ኢየሱስ፡ነው፡አሉ። 12፤ኢየሱስም፡ወደ፡መቅደስ፡ገባና፡በመቅደስ፡የሚሸጡትንና፡የሚገዙትን፡ዅሉ፡አወጣ፥የገንዘብ፡ ለዋጮችንም፡ገበታዎች፡የርግብ፡ሻጪዎችንም፡ወንበሮች፡ገለበጠና፦ 13፤ቤቴ፡የጸሎት፡ቤት፡ትባላለች፡ተብሎ፡ተጽፏል፥እናንተ፡ግን፡የወንበዴዎች፡ዋሻ፡አደረጋችዃት፡ አላቸው። 14፤በመቅደስም፡ዕውሮችና፡ዐንካሳዎች፡ወደ፡ርሱ፡ቀረቡና፡ፈወሳቸው። 15፤ነገር፡ግን፥የካህናት፡አለቃዎችና፡ጻፊዎች፡ያደረገውን፡ድንቃ፡ድንቅ፡በመቅደስም፦ሆሣዕና፡ለዳዊት፡ልጅ፡እያሉ፡የሚጮኹትን፡ልጆች፡ባዩ፡ጊዜ፥ተቈጥተው። 16፤እነዚህ፡የሚሉትን፡አትሰማምን፧አሉት።ኢየሱስም፦እሰማለኹ፤ከሕፃናትና፡ከሚጠቡት፡አፍ፡ምስጋናን፡ ለራስኽ፡አዘጋጀኽ፡የሚለውን፡ቃል፡ከቶ፡አላነበባችኹምን፧አላቸው። 17፤ትቷቸውም፡ከከተማ፡ወደ፡ቢታንያ፡ወጣ፡በዚያም፡ዐደረ። 18፤በማለዳም፡ወደ፡ከተማ፡ሲመለስ፡ተራበ። 19፤በመንገድም፡አጠገብ፡በለስ፡አይቶ፡ወደ፡ርሷ፡መጣ፤ከቅጠልም፡ብቻ፡በቀር፡ምንም፡ አላገኘባትምና፦ለዘለዓለሙ፡ፍሬ፡አይገኝብሽ፡አላት።በለሲቱም፡ያን፡ጊዜውን፡ደረቀች። 20፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ይህን፡አይተው፦በለሲቱ፡ያን፡ጊዜውን፡እንዴት፡ደረቀች፧ብለው፡ተደነቁ። 21፤ኢየሱስም፡መልሶ፦እውነት፡እላችዃለኹ፥እምነት፡ቢኖራችኹ፡ባትጠራጠሩም፥በበለሲቱ፡እንደ፡ኾነባት፡ ብቻ፡አታደርጉም፤ነገር፡ግን፥ይህን፡ተራራ፡እንኳ፦ተነቅለኽ፡ወደ፡ባሕር፡ተወርወር፡ብትሉት፡ይኾናል፤ 22፤አምናችኹም፡በጸሎት፡የምትለምኑትን፡ዅሉ፡ትቀበላላችኹ፡አላቸው። 23፤ወደ፡መቅደስም፡ገብቶ፡ሲያስተምር፡የካህናት፡አለቃዎችና፡የሕዝብ፡ሽማግሌዎች፡ወደ፡ርሱ፡ ቀረቡና፦በምን፡ሥልጣን፡እነዚህን፡ታደርጋለኽ፧ይህንስ፡ሥልጣን፡ማን፡ሰጠኽ፧አሉት። 24፤ኢየሱስም፡መልሶ፦እኔ፡ደግሞ፡አንዲት፡ነገር፡እጠይቃችዃለኹ፤እናንተም፡ያችን፡ብትነግሩኝ፡እኔ፡ ደግሞ፡እነዚህን፡በምን፡ሥልጣን፡እንዳደርግ፡እነግራችዃለኹ፤ 25፤የዮሐንስ፡ጥምቀት፡ከወዴት፡ነበረች፧ከሰማይን፡ወይስ፡ከሰው፧አላቸው።እነርሱም፡ርስ፡በርሳቸው፡ ሲነጋገሩ፦ከሰማይ፡ብንል፦እንኪያስ፡ስለ፡ምን፡አላመናችኹበትም፧ይለናል፤ 26፤ከሰው፡ግን፡ብንል፥ዮሐንስን፡ዅሉም፡እንደ፡ነቢይ፡ያዩታልና፥ሕዝቡን፡እንፈራለን፡አሉ። 27፤ለኢየሱስም፡መልሰው፦አናውቅም፡አሉት።ርሱም፡ደግሞ፦እኔም፡በምን፡ሥልጣን፡እነዚህን፡እንዳደርግ፡ አልነግራችኹም፡አላቸው። 28፤ነገር፡ግን፥ምን፡ይመስላችዃል፧አንድ፡ሰው፡ኹለት፡ልጆች፡ነበሩት፤ወደ፡አንደኛው፡ቀርቦ፦ልጄ፡ ሆይ፥ዛሬ፡ኺድና፡በወይኔ፡አትክልት፡ሥራ፡አለው። 29፤ርሱም፡መልሶ፦አልወድም፡አለ፤ዃላ፡ግን፡ተጸጸተና፡ኼደ። 30፤ወደ፡ኹለተኛውም፡ቀርቦ፡እንዲሁ፡አለው፡ርሱም፡መልሶ፦ዕሺ፡ጌታዬ፡አለ፤ነገር፡ግን፥አልኼደም። 31፤ከኹለቱ፡የአባቱን፡ፈቃድ፡ያደረገ፡ማን፡ነው፧ፊተኛው፡አሉት።ኢየሱስ፡እንዲህ፡አላቸው፦እውነት፡ እላችዃለኹ፥ቀራጮችና፡ጋለሞታዎች፡ወደእግዚአብሔር፡መንግሥት፡በመግባት፡ይቀድሟችዃል። 32፤ዮሐንስ፡በጽድቅ፡መንገድ፡መጥቶላችኹ፡ነበርና፥አላመናችኹበትም፤ቀራጮችና፡ጋለሞታዎች፡ግን፡ አመኑበት፤እናንተም፡ይህን፡አይታችኹ፡ታምኑበት፡ዘንድ፡በዃላ፡ንስሓ፡አልገባችኹም። 33፤ሌላ፡ምሳሌ፡ስሙ።የወይን፡አትክልት፡የተከለ፡ባለቤት፡ሰው፡ነበረ፤ቅጥርም፡ቀጠረለት፥መጥመቂያም፡ ማሰለት፥ግንብም፡ሠራና፡ለገበሬዎች፡አከራይቶ፡ወደ፡ሌላ፡አገር፡ኼደ። 34፤የሚያፈራበትም፡ጊዜ፡ሲቀርብ፥ፍሬውን፡ሊቀበሉ፡ባሮቹን፡ወደ፡ገበሬዎች፡ላከ። 35፤ገበሬዎቹም፡ባሮቹን፡ይዘው፡አንዱን፡ደበደቡት፡አንዱንም፡ገደሉት፡ሌላውንም፡ወገሩት። 36፤ደግሞ፡ከፊተኛዎች፡የሚበዙ፡ሌላዎች፡ባሪያዎችን፡ላከ፥እንዲሁም፡አደረጉባቸው። 37፤በዃላ፡ግን፦ልጄንስ፡ያፍሩታል፡ብሎ፡ልጁን፡ላከባቸው። 38፤ገበሬዎቹ፡ግን፡ልጁን፡ባዩ፡ጊዜ፡ርስ፡በርሳቸው፦ወራሹ፡ይህ፡ነው፤ኑ፥እንግደለውና፡ርስቱን፡ እናግኝ፡ተባባሉ። 39፤ይዘውም፡ከወይኑ፡አትክልት፡አወጡና፡ገደሉት። 40፤እንግዲህ፡የወይኑ፡አትክልት፡ጌታ፡በሚመጣ፡ጊዜ፡በእነዚህ፡ገበሬዎች፡ምን፡ያደርግባቸዋል፧ 41፤እነርሱም፦ክፉዎችን፡በክፉ፡ያጠፋቸዋል፥የወይኑንም፡አትክልት፡ፍሬውን፡በየጊዜው፡ለሚያስረክቡ፡ ለሌላዎች፡ገበሬዎች፡ይሰጠዋል፡አሉት። 42፤ኢየሱስ፡እንዲህ፡አላቸው፦ግንበኛዎች፡የናቁት፡ድንጋይ፡ርሱ፡የማእዘን፡ራስ፡ኾነ፤ይህም፡ከጌታ፡ ዘንድ፡ኾነ፥ለዐይኖቻችንም፡ድንቅ፡ነው፡የሚለውን፡ከቶ፡በመጽሐፍ፡አላነበባችኹምን፧ 43፤ስለዚህ፥እላችዃለኹ፥የእግዚአብሔር፡መንግሥት፡ከእናንተ፡ትወሰዳለች፥ፍሬዋንም፡ለሚያደርግ፡ሕዝብ፡ ትሰጣለች። 44፤በዚህም፡ድንጋይ፡ላይ፡የሚወድቅ፡ይቀጠቀጣል፤ድንጋዩ፡ግን፡የሚወድቅበትን፡ዅሉ፡ይፈጨዋል። 45፤የካህናት፡አለቃዎችና፡ፈሪሳውያንም፡ምሳሌዎቹን፡ሰምተው፡ስለ፡እነርሱ፡እንደ፡ተናገረ፡አስተዋሉ፤ 46፤ሊይዙትም፡ሲፈልጉት፡ሳሉ፡ሕዝቡ፡እንደ፡ነቢይ፡ስላዩት፡ፈሯቸው።

ምዕራፍ ፳፪

1፤ኢየሱስም፡መለሰ፡ደግሞም፡በምሳሌ፡ነገራቸው፡እንዲህም፡አለ፦ 2፤መንግሥተ፡ሰማያት፡ለልጁ፡ሰርግ፡ያደረገ፡ንጉሥን፡ትመስላለች። 3፤የታደሙትንም፡ወደ፡ሰርጉ፡ይጠሩ፡ዘንድ፡ባሮቹን፡ላከ፡ሊመጡም፡አልወደዱም። 4፤ደግሞ፡ሌላዎችን፡ባሪያዎች፡ልኮ፦የታደሙትን፦እንሆ፥ድግሴን፡አዘጋጀኹ፥ኰርማዎቼና፡የሰቡት፡ ከብቶቼ፡ታርደዋል፥ዅሉም፡ተዘጋጅቷል፤ወደ፡ሰርጉ፡ኑ፡በሏቸው፡አለ። 5፤እነርሱ፡ግን፡ቸል፡ብለው፡አንዱ፡ወደ፡ዕርሻው፥ሌላውም፡ወደ፡ንግዱ፡ኼደ፤ 6፤የቀሩትም፡ባሮቹን፡ይዘው፡አንገላቷቸው፡ገደሏቸውም። 7፤ንጉሡም፡ተቈጣ፥ጭፍራዎቹንም፡ልኮ፡እነዚያን፡ገዳዮች፡አጠፋ፤ከተማቸውንም፡አቃጠለ። 8፤በዚያን፡ጊዜ፡ባሮቹን፦ሰርጉስ፡ተዘጋጅቷል፥ነገር፡ግን፥የታደሙት፡የማይገ፟ባ፟ቸው፡ኾኑ፤ 9፤እንግዲህ፡ወደመንገድ፡መተላለፊያ፡ኼዳችኹ፡ያገኛችኹትን፡ዅሉ፡ወደ፡ሰርጉ፡ጥሩ፡አለ። 10፤እነዚያም፡ባሪያዎች፡ወደ፡መንገድ፡ወጥተው፡ያገኙትን፡ዅሉ፡ክፉዎችንም፡በጎዎችንም፡ ሰበሰቡ፤የሰርጉንም፡ቤት፡ተቀማጮች፡ሞሉት። 11፤ንጉሡም፡የተቀመጡትን፡ለማየት፡በገባ፡ጊዜ፡በዚያ፡የሰርግ፡ልብስ፡ያለበሰ፡አንድ፡ሰው፡አየና፦ወዳጄ፡ ሆይ፥ 12፤የሰርግ፡ልብስ፡ሳትለብስ፡እንዴት፡ወደዚህ፡ገባኽ፧አለው፡ርሱም፡ዝም፡አለ። 13፤በዚያን፡ጊዜ፡ንጉሡ፡አገልጋዮቹን፦እጁንና፡እግሩን፡አስራችኹ፡በውጭ፡ወዳለው፡ጨለማ፡ አውጡት፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡ይኾናል፡አለ። 14፤የተጠሩ፡ብዙዎች፥የተመረጡ፡ግን፡ጥቂቶች፡ናቸውና። 15፤ስለዚህ፥ፈሪሳውያን፡ኼዱና፥እንዴት፡አድርገው፡በነገር፡እንዲያጠምዱት፡ተማከሩ። 16፤ደቀ፡መዛሙርታቸውንም፡ከሄሮድስ፡ወገን፡ጋራ፡ላኩበት፥እነርሱም፦መምህር፡ሆይ፥እውነተኛ፡እንደ፡ ኾንኽ፡በእውነትም፡የእግዚአብሔርን፡መንገድ፡እንድታስተምር፡እናውቃለን፥ለማንምም፡አታደላም፥የሰውን፡ ፊት፡አትመለከትምና፤ 17፤እንግዲህ፡ምን፡ይመስልኻል፧ንገረን፡ለቄሳር፡ግብር፡መስጠት፡ተፈቅዷልን፡ወይስ፡አልተፈቀደም፧አሉት። 18፤ኢየሱስም፡ክፋታቸውን፡ዐውቆ፦እናንተ፡ግብዞች፥ስለ፡ምን፡ትፈትኑኛላችኹ፧ 19፤የግብሩን፡ብር፡አሳዩኝ፡አለ።እነርሱም፡ዲናር፡አመጡለት። 20፤ርሱም፦ይህች፡መልክ፡ጽሕፈቲቱስ፡የማን፡ናት፧አላቸው። 21፤የቄሳር፡ነው፡አሉት።በዚያን፡ጊዜ፦እንኪያስ፡የቄሳርን፡ለቄሳር፡የእግዚአብሔርንም፡ለእግዚአብሔር፡ አስረክቡ፡አላቸው። 22፤ይህንም፡ሰምተው፡ተደነቁ፥ትተውትም፡ኼዱ። 23፤በዚያን፡ቀን፦ትንሣኤ፡ሙታን፡የለም፡የሚሉ፡ሰዱቃውያን፡ወደ፡ርሱ፡ቀረቡ፥ 24፤እንዲህም፡ብለው፡ጠየቁት፦መምህር፡ሆይ፥ሙሴ፡አንድ፡ሰው፡ልጅ፡ሳይወልድ፡ሲሞት፡ወንድሙ፡ ሚስቱን፡አግብቶ፡ለወንድሙ፡ዘር፡ይተካ፡አለ። 25፤ሰባት፡ወንድማማች፡በእኛ፡ዘንድ፡ነበሩ፤ፊተኛውም፡ሚስት፡አግብቶ፡ሞተ፥ዘርም፡ስለሌለው፡ሚስቱን፡ ለወንድሙ፡ተወለት፤ 26፤እንዲሁ፡ደግሞ፡ኹለተኛው፡ሦስተኛውም፥እስከ፡ሰባተኛው፡ድረስ። 27፤ከዅሉም፡በዃላ፡ሴቲቱ፡ሞተች። 28፤ዅሉ፡አግብተዋታልና፥በትንሣኤ፡ቀንስ፥ከሰባቱ፡ለማናቸው፡ሚስት፡ትኾናለች፧ 29፤ኢየሱስም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦መጻሕፍትንና፡የእግዚአብሔርን፡ኀይል፡አታውቁምና፡ትስታላችኹ። 30፤በትንሣኤስ፡እንደእግዚአብሔር፡መላእክት፡በሰማይ፡ይኾናሉ፡እንጂ፡አያገቡም፡አይጋቡምም። 31-32፤ስለ፡ትንሣኤ፡ሙታን፡ግን፦እኔ፡የአብርሃም፡አምላክ፥የይሥሐቅም፡አምላክ፡የያዕቆብም፡አምላክ፡ ነኝ፡የሚል፡ከእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ወደ፡እናንተ፡የተባለውን፡አላነበባችኹምን፧የሕያዋን፡አምላክ፡ነው፡ እንጂ፡የሙታን፡አይደለም። 33፤ሕዝቡም፡ይህን፡ሰምተው፡በትምህርቱ፡ተገረሙ። 34፤ፈሪሳውያንም፡ሰዱቃውያንን፡ዝም፡እንዳሠኛቸው፡በሰሙ፡ጊዜ፡ዐብረው፡ተሰበሰቡ። 35፤ከነርሱም፡አንድ፡ሕግ፡ዐዋቂ፡ሊፈትነው። 36፤መምህር፡ሆይ፥ከሕግ፡ማናቸዪቱ፡ትእዛዝ፡ታላቅ፡ናት፧ብሎ፡ጠየቀው። 37፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አለው፦ጌታ፡አምላክኽን፡በፍጹም፡ልብኽ፡በፍጹም፡ነፍስኽም፡በፍጹም፡ዐሳብኽም፡ ውደድ። 38፤ታላቂቱና፡ፊተኛዪቱ፡ትእዛዝ፡ይህች፡ናት። 39፤ኹለተኛዪቱም፡ይህችን፡ትመስላለች፥ርሷም፦ባልንጀራኽን፡እንደ፡ነፍስኽ፡ውደድ፡የምትለው፡ናት። 40፤በእነዚህ፡በኹለቱ፡ትእዛዛት፡ሕጉም፡ዅሉ፡ነቢያትም፡ተሰቅለዋል። 41-42፤ፈሪሳውያንም፡ተሰብስበው፡ሳሉ፥ኢየሱስ፦ስለ፡ክርስቶስ፡ምን፡ይመስላችዃል፧የማንስ፡ልጅ፡ ነው፧ብሎ፡ጠየቃቸው፦የዳዊት፡ልጅ፡ነው፡አሉት። 43-44፤ርሱም፦እንኪያስ፡ዳዊት፦ጌታ፡ጌታዬን፦ጠላቶችኽን፡የእግርኽ፡መረገጫ፡እስካደርግልኽ፡ድረስ፡ በቀኜ፡ተቀመጥ፡አለው፡ሲል፡እንዴት፡በመንፈስ፡ጌታ፡ብሎ፡ይጠራዋል፧ 45፤ዳዊትስ፡ጌታ፡ብሎ፡ከጠራው፥እንዴት፡ልጁ፡ይኾናል፧አላቸው። 46፤አንድም፡ቃል፡ስንኳ፡ይመልስለት፡ዘንድ፡የተቻለው፡የለም፥ከዚያ፡ቀንም፡ዠምሮ፡ወደ፡ፊት፡ማንም፡ሊጠይቀው፡አልደፈረም።

ምዕራፍ ፳፫

1፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡ለሕዝቡና፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡እንዲህ፡ብሎ፡ነገራቸው፦ 2፤ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፡በሙሴ፡ወንበር፡ተቀምጠዋል። 3፤ስለዚህ፥ያዘዟችኹን፡ዅሉ፡አድርጉ፥ጠብቁትም፤ነገር፡ግን፥እየተናገሩ፡አያደርጉትምና፥እንደ፡ሥራቸው፡ አታድርጉ። 4፤ከባድና፡አስቸጋሪ፡ሸክም፡ተብትበው፡በሰው፡ትከሻ፡ይጭናሉ፥እነርሱ፡ግን፡በጣታቸው፡ስንኳ፡ሊነኩት፡ አይወዱም። 5፤ለሰውም፡እንዲታዩ፡ሥራቸውን፡ዅሉ፡ያደርጋሉ፤ስለዚህ፥ዐሸን፡ክታባቸውን፡ያሰፋሉ፥ዘርፉንም፡ ያስረዝማሉ፥ 6፤በምሳም፡የከበሬታ፡ስፍራ፥በምኵራብም፡የከበሬታ፡ወንበር፥ 7፤በገበያም፡ሰላምታና፦መምህር፡ሆይ፡መምህር፡ሆይ፡ተብለው፡እንዲጠሩ፡ይወዳሉ። 8፤እናንተ፡ግን፦መምህር፡ተብላችኹ፡አትጠሩ፤መምህራችኹ፡አንድ፡ስለ፡ኾነ፡እናንተም፡ዅላችኹ፡ ወንድማማች፡ናችኹ። 9፤አባታችኹ፡አንዱ፡ርሱም፡የሰማዩ፡ነውና፥በምድር፡ላይ፡ማንንም፦አባት፡ብላችኹ፡አትጥሩ። 10፤ሊቃችኹ፡አንድ፡ርሱም፡ክርስቶስ፡ነውና፦ሊቃውንት፡ተብላችኹ፡አትጠሩ። 11፤ከእናንተም፡የሚበልጠው፡አገልጋያችኹ፡ይኾናል። 12፤ራሱን፡ከፍ፡የሚያደርግ፡ዅሉ፡ይዋረዳል፥ራሱንም፡የሚያዋርድ፡ዅሉ፡ከፍ፡ይላል። 13፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥መንግሥተ፡ሰማያትን፡በሰው፡ፊት፡ስለምትዘጉ፥ወዮላችኹ፡ እናንተ፡አትገቡም፡የሚገቡትንም፡እንዳይገቡ፡ትከለክላላችኹ። 14፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥በጸሎት፡ርዝመት፡እያመካኛችኹ፡የመበለቶችን፡ቤት፡ ስለምትበሉ፥ወዮላችኹ፤ስለዚህ፥የባሰ፡ፍርድ፡ትቀበላላችኹ። 15፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥አንድ፡ሰው፡ልታሳምኑ፡በባሕርና፡በደረቅ፡ስለምትዞሩ፥በኾነም፡ ጊዜ፡ከእናንተ፡ይልቅ፡ኹለት፡ዕጥፍ፡የባሰ፡የገሃነም፡ልጅ፡ስለምታደርጉት፥ወዮላችኹ። 16፤እናንተ፦ማንም፡በቤተ፡መቅደስ፡የሚምል፡ምንም፡የለበትም፤ማንም፡በቤተ፡መቅደስ፡ወርቅ፡የሚምል፡ ግን፡በመሐላው፡ይያዛል፡የምትሉ፥ዕውሮች፡መሪዎች፥ወዮላችኹ። 17፤እናንተ፡ደንቈሮዎችና፡ዕውሮች፥ማናቸው፡ይበልጣል፧ወርቁ፡ነውን፧ወይስ፡ወርቁን፡የቀደሰው፡ቤተ፡ መቅደስ፧ 18፤ደግማችኹም፦ማንም፡በመሠዊያው፡የሚምል፡ምንም፡የለበትም፤ማንም፡በላዩ፡ባለው፡መባ፡የሚምል፡ ግን፡በመሐላው፡ይያዛል፡ትላላችኹ። 19፤እናንተ፡ደንቈሮዎችና፡ዕውሮች፥ማናቸው፡ይበልጣል፧መባው፡ነውን፧ወይስ፡መባውን፡የሚቀድሰው፡ መሠዊያው፧ 20፤እንግዲህ፡በመሠዊያው፡የሚምለው፡በርሱና፡በርሱ፡ላይ፡ባለው፡ዅሉ፡ይምላል፤ 21፤በቤተ፡መቅደስም፡የሚምለው፡በርሱና፡በርሱ፡በሚኖረው፡ይምላል፤ 22፤በሰማይም፡የሚምለው፡በእግዚአብሔር፡ዙፋንና፡በርሱ፡ላይ፡በተቀመጠው፡ይምላል። 23፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥ከአዝሙድና፡ከእንስላል፡ከከሙንም፡ዓሥራት፡ ስለምታወጡ፥ፍርድንና፡ምሕረትን፡ታማኝነትንም፥በሕግ፡ያለውን፡ዋና፡ነገር፡ ስለምትተዉ፥ወዮላችኹ፤ሌላውን፡ሳትተዉ፡ይህን፡ልታደርጉ፡ይገ፟ባ፟ችኹ፡ነበር። 24፤እናንተ፡ዕውሮች፡መሪዎች፥ትንኝን፡የምታጠሩ፡ግመልንም፡የምትውጡ። 25፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥በውስጡ፡ቅሚያና፡ሥሥት፡ሞልቶ፡ሳለ፡የጽዋውንና፡የወጭቱን፡ ውጭ፡ስለምታጠሩ፥ወዮላችኹ። 26፤አንተ፡ዕውር፡ፈሪሳዊ፥ውጭው፡ደግሞ፡ጥሩ፡እንዲኾን፡አስቀድመኽ፡የጽዋውንና፡የወጭቱን፡ውስጡን፡ አጥራ። 27፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥በውጭ፡አምረው፡የሚታዩ፡በውስጡ፡ግን፡የሙታን፡ዐጥንት፡ ርኵሰትም፡ዅሉ፡የተሞሉ፡በኖራ፡የተለሰኑ፡መቃብሮችን፡ስለምትመስሉ፥ወዮላችኹ። 28፤እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡በውጭ፡ለሰው፡እንደ፡ጻድቃን፡ትታያላችኹ፥በውስጣችኹ፡ግን፡ግብዝነትና፡ ዐመፀኝነት፡ሞልቶባችዃል። 29፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥የነቢያትን፡መቃብር፡ስለምትሠሩ፡የጻድቃንንም፡መቃብር፡ ስለምታስጌጡና፦ 30፤በአባቶቻችን፡ዘመን፡ኖረን፡በኾነስ፥በነቢያት፡ደም፡ባልተባበርናቸውም፡ነበር፡ስለምትሉ፥ወዮላችኹ። 31፤እንግዲያስ፡የነቢያት፡ገዳዮች፡ልጆች፡እንደኾናችኹ፡በራሳችኹ፡ላይ፡ትመሰክራላችኹ። 32፤እናንተ፡ደግሞ፡የአባቶቻችኹን፡መስፈሪያ፡ሙሉ። 33፤እናንተ፡እባቦች፥የእፍኝት፡ልጆች፥ከገሃነም፡ፍርድ፡እንዴት፡ታመልጣላችኹ፧ 34፤ስለዚህ፥እንሆ፥ነቢያትንና፡ጥበበኛዎችን፡ጻፊዎችንም፡ወደ፡እናንተ፡እልካለኹ፤ከነርሱም፡ትገድላላችኹ፡ ትሰቅሉማላችኹ፥ከነርሱም፡በምኵራባችኹ፡ትገርፋላችኹ፡ከከተማም፡ወደ፡ከተማ፡ታሳድዳላችኹ፤ 35፤ከጻድቁ፡ከአቤል፡ደም፡ዠምሮ፡በቤተ፡መቅደስና፡በመሠዊያው፡መካከል፡እስከገደላችኹት፡እስከበራክዩ፡ ልጅ፡እስከዘካርያስ፡ደም፡ድረስ፡በምድር፡ላይ፡የፈሰሰው፡የጻድቅ፡ደም፡ዅሉ፡ይደርስባችኹ፡ዘንድ። 36፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ይህ፡ዅሉ፡በዚህ፡ትውልድ፡ላይ፡ይደርሳል። 37፤ኢየሩሳሌም፡ኢየሩሳሌም፡ሆይ፥ነቢያትን፡የምትገድል፡ወደ፡ርሷ፡የተላኩትንም፡የምትወግር፥ዶሮ፡ ጫጩቶቿን፡ከክንፎቿ፡በታች፡እንደምትሰበስብ፡ልጆችሽን፡እሰበስብ፡ዘንድ፡ስንት፡ጊዜ፡ወደድኹ! አልወደዳችኹምም። 38፤እንሆ፥ቤታችኹ፡የተፈታ፡ኾኖ፡ይቀርላችዃል። 39፤እላችዃለኹና፥በጌታ፡ስም፡የሚመጣ፡የተባረከ፡ነው፡እስክትሉ፡ድረስ፡ከእንግዲህ፡ወዲህ፡አታዩኝም።

ምዕራፍ ፳፬

1፤ኢየሱስም፡ከመቅደስ፡ወጥቶ፡ኼደ፥ደቀ፡መዛሙርቱም፡የመቅደሱን፡ግንቦች፡ሊያሳዩት፡ቀረቡ። 2፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፦ይህን፡ዅሉ፡ታያላችኹን፧እውነት፡እላችዃለኹ፥ድንጋይ፡በድንጋይ፡ላይ፡ሳይፈርስ፡ በዚህ፡አይቀርም፡አላቸው። 3፤ርሱም፡በደብረ፡ዘይት፡ተቀምጦ፡ሳለ፥ደቀ፡መዛሙርቱ፡ለብቻቸው፡ወደ፡ርሱ፡ቀርበው፦ንገረን፥ይህ፡ መቼ፡ይኾናል፧የመምጣትኽና፡የዓለም፡መጨረሻ፡ምልክቱስ፡ምንድር፡ነው፧አሉት። 4፤ኢየሱስም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላቸው፦ማንም፡እንዳያስታችኹ፡ተጠንቀቁ። 5፤ብዙዎች፦እኔ፡ክርስቶስ፡ነኝ፡እያሉ፡በስሜ፡ይመጣሉና፤ብዙዎችንም፡ያስታሉ። 6፤ጦርንም፡የጦርንም፡ወሬ፡ትሰሙ፡ዘንድ፡አላችኹ፤ይህ፡ሊኾን፡ግድ፡ነውና፥ተጠበቁ፥አትደንግጡ፤ዳሩ፡ ግን፡መጨረሻው፡ገና፡ነው። 7፤ሕዝብ፡በሕዝብ፡ላይ፡መንግሥትም፡በመንግሥት፡ላይ፡ይነሣልና፥ራብም፡ቸነፈርም፡የምድርም፡መናወጥ፡ በልዩ፡ልዩ፡ስፍራ፡ይኾናል፤ 8፤እነዚህም፡ዅሉ፡የምጥ፡ጣር፡መዠመሪያ፡ናቸው። 9፤በዚያን፡ጊዜ፡ለመከራ፡አሳልፈው፡ይሰጧችዃል፡ይገድሏችኹማል፥ስለ፡ስሜም፡በአሕዛብ፡ዅሉ፡ የተጠላችኹ፡ትኾናላችኹ። 10፤በዚያን፡ጊዜም፡ብዙዎች፡ይሰናከላሉ፡ርስ፡በርሳቸውም፡አሳልፈው፡ይሰጣጣሉ፥ርስ፡በርሳቸውም፡ይጣላሉ፤ 11፤ብዙ፡ሐሰተኛዎች፡ነቢያትም፡ይነሣሉ፡ብዙዎችንም፡ያስታሉ፤ 12፤ከዐመፃም፡ብዛት፡የተነሣ፡የብዙ፡ሰዎች፡ፍቅር፡ትቀዘቅዛለች። 13፤እስከ፡መጨረሻ፡የሚጸና፡ግን፡ርሱ፡ይድናል። 14፤ለአሕዛብም፡ዅሉ፡ምስክር፡እንዲኾን፡ይህ፡የመንግሥት፡ወንጌል፡በዓለም፡ዅሉ፡ይሰበካል፥በዚያን፡ ጊዜም፡መጨረሻው፡ይመጣል። 15፤እንግዲህ፡በነቢዩ፡በዳንኤል፡የተባለውን፡የጥፋትን፡ርኵሰት፡በተቀደሰችው፡ስፍራ፡ቆሞ፡ስታዩ፥አንባቢው፡ ያስተውል፥ 16፤በዚያን፡ጊዜ፡በይሁዳ፡ያሉት፡ወደ፡ተራራዎች፡ይሽሹ፥ 17፤በሰገነትም፡ያለ፡በቤቱ፡ያለውን፡ሊወስድ፡አይውረድ፥ 18፤በዕርሻም፡ያለ፡ልብሱን፡ይወስድ፡ዘንድ፡ወደ፡ዃላው፡አይመለስ። 19፤በዚያችም፡ወራት፡ለርጕዞችና፡ለሚያጠቡ፡ወዮላቸው። 20፤ነገር፡ግን፥ሽሽታችኹ፡በክረምት፡ወይም፡በሰንበት፡እንዳይኾን፡ጸልዩ፤ 21፤በዚያን፡ጊዜ፡ከዓለም፡መዠመሪያ፡ዠምሮ፡እስከ፡ዛሬ፡ድረስ፡ያልኾነ፡እንግዲህም፡ከቶ፡የማይኾን፡ ታላቅ፡መከራ፡ይኾናልና። 22፤እነዚያ፡ቀኖችስ፡ባያጥሩ፡ሥጋ፡የለበሰ፡ዅሉ፡ባልዳነም፡ነበር፤ነገር፡ግን፥እነዚያ፡ቀኖች፡ ስለተመረጡት፡ሰዎች፡ያጥራሉ። 23፤በዚያን፡ጊዜ፡ማንም፦እንሆ፥ክርስቶስ፡ከዚህ፡አለ፡ወይም፦ከዚያ፡አለ፡ቢላችኹ፡አትመኑ፤ 24፤ሐሰተኛዎች፡ክርስቶሶችና፡ሐሰተኛዎች፡ነቢያት፡ይነሣሉና፥ቢቻላቸውስ፡የተመረጡትን፡እንኳ፡እስኪያስቱ፡ ድረስ፡ታላላቅ፡ምልክትና፡ድንቅ፡ያሳያሉ። 25፤እንሆ፥አስቀድሜ፡ነገርዃችኹ። 26፤እንግዲህ፦እንሆ፥በበረሓ፡ነው፡ቢሏችኹ፥አትውጡ፤እንሆ፥በዕልፍኝ፡ነው፡ቢሏችኹ፥አትመኑ፤ 27፤መብረቅ፡ከምሥራቅ፡ወጥቶ፡እስከ፡ምዕራብ፡እንደሚታይ፥የሰው፡ልጅ፡መምጣት፡እንዲሁ፡ይኾናልና፤ 28፤በድን፡ወዳለበት፡በዚያ፡አሞራዎች፡ይሰበሰባሉ። 29፤ከዚያች፡ወራትም፡መከራ፡በዃላ፡ወዲያው፡ፀሓይ፡ይጨልማል፥ጨረቃም፡ብርሃኗን፡ አትሰጥም፥ከዋክብትም፡ከሰማይ፡ይወድቃሉ፥ 30፤የሰማያትም፡ኀይላት፡ይናወጣሉ።በዚያን፡ጊዜም፡የሰው፡ልጅ፡ምልክት፡በሰማይ፡ይታያል፥በዚያን፡ ጊዜም፡የምድር፡ወገኖች፡ዅሉ፡ዋይ፡ዋይ፡ይላሉ፥የሰው፡ልጅንም፡በኀይልና፡በብዙ፡ክብር፡በሰማይ፡ደመና፡ ሲመጣ፡ያዩታል፤ 31፤መላእክቱንም፡ከታላቅ፡መለከት፡ድምፅ፡ጋራ፡ይልካቸዋል፥ከሰማያትም፡ዳርቻ፡እስከ፡ዳርቻው፡ከአራቱ፡ ነፋሳት፡ለርሱ፡የተመረጡትን፡ይሰበስባሉ። 32፤ምሳሌውንም፡ከበለስ፡ተማሩ፤ጫፏ፡ሲለሰልስ፡ቅጠሏም፡ሲያቈጠቍጥ፥ያን፡ጊዜ፡በጋ፡እንደ፡ቀረበ፡ ታውቃላችኹ፤ 33፤እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡ይህን፡ዅሉ፡ስታዩ፡በደጅ፡እንደ፡ቀረበ፡ዕወቁ። 34፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ይህ፡ዅሉ፡እስኪኾን፡ድረስ፡ይህ፡ትውልድ፡አያልፍም። 35፤ሰማይና፡ምድር፡ያልፋሉ፥ቃሌ፡ግን፡አያልፍም። 36፤ስለዚያች፡ቀንና፡ስለዚያች፡ሰዓት፡ግን፡ከአባት፡ብቻ፡በቀር፡የሰማይ፡መላእክትም፡ቢኾኑ፡ልጅም፡ ቢኾን፡የሚያውቅ፡የለም። 37፤የኖኅ፡ዘመን፡እንደ፡ነበረ፡የሰው፡ልጅ፡መምጣት፡እንዲሁ፡ይኾናልና። 38፤በዚያች፡ወራት፡ከጥፋት፡ውሃ፡በፊት፥ኖኅ፡ወደ፡መርከብ፡እስከገባበት፡ቀን፡ድረስ፥ሲበሉና፡ሲጠጡ፡ ሲያገቡና፡ሲጋቡም፡እንደ፡ነበሩ፥ 39፤የጥፋት፡ውሃም፡መጥቶ፡ዅሉን፡እስከወሰደ፡ድረስ፡እንዳላወቁ፥የሰው፡ልጅ፡መምጣት፡ደግሞ፡እንዲሁ፡ ይኾናል። 40፤በዚያን፡ጊዜ፡ኹለት፡ሰዎች፡በዕርሻ፡ይኾናሉ፤አንዱ፡ይወሰዳል፡አንዱም፡ይቀራል፤ 41፤ኹለት፡ሴቶች፡በወፍጮ፡ይፈጫሉ፤አንዲቱ፡ትወሰዳለች፡አንዲቱም፡ትቀራለች። 42፤ጌታችኹ፡በምን፡ሰዓት፡እንዲመጣ፡አታውቁምና፡እንግዲህ፡ንቁ። 43፤ያን፡ግን፡ዕወቁ፤ባለቤት፡ከሌሊቱ፡በየትኛው፡ክፍል፡ሌባ፡እንዲመጣ፡ቢያውቅ፡ኖሮ፥በነቃ፡ቤቱም፡ ሊቈፈር፡ባልተወም፡ነበር። 44፤ስለዚህ፥እናንተ፡ደግሞ፡ተዘጋጅታችኹ፡ኑሩ፥የሰው፡ልጅ፡በማታስቡበት፡ሰዓት፡ይመጣልና። 45፤እንኪያስ፡ምግባቸውን፡በጊዜው፡ይሰጣቸው፡ዘንድ፡ጌታው፡በቤተ፡ሰዎች፡ላይ፡የሾመው፡ታማኝና፡ ልባም፡ባሪያ፡ማን፡ነው፧ 46፤ጌታው፡መጥቶ፡እንዲህ፡ሲያደርግ፡የሚያገኘው፡ያ፡ባሪያ፡ብፁዕ፡ነው፤ 47፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ባለው፡ዅሉ፡ላይ፡ይሾመዋል። 48፤ያ፡ክፉ፡ባሪያ፡ግን፦ጌታዬ፡እስኪመጣ፡ይዘገያል፡ብሎ፡በልቡ፡ቢያስብ፥ 49፤ባልንጀራዎቹን፡ባሪያዎች፡ሊመታ፡ቢዠምር፥ከሰካሮችም፡ጋራ፡ቢበላና፡ቢጠጣ፥ 50፤የዚያ፡ባሪያ፡ጌታ፡ባልጠበቃት፡ቀን፡ባላወቃትም፡ሰዓት፡ይመጣል፥ 51፤ከኹለትም፡ይሰነጥቀዋል፥ዕድሉንም፡ከግብዞች፡ጋራ፡ያደርግበታል፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡ ይኾናል።

ምዕራፍ ፳፭

1፤በዚያን፡ጊዜ፡መንግሥተ፡ሰማያት፡መብራታቸውን፡ይዘው፡ሙሽራውን፡ሊቀበሉ፡የወጡ፡ዐሥር፡ ቈነዣዥትን፡ትመስላለች። 2፤ከነርሱም፡ዐምስቱ፡ሰነፎች፡ዐምስቱም፡ልባሞች፡ነበሩ። 3፤ሰነፎቹ፡መብራታቸውን፡ይዘው፡ከነርሱ፡ጋራ፡ዘይት፡አልያዙምና፤ 4፤ልባሞቹ፡ግን፡ከመብራታቸው፡ጋራ፡በማሰሯቸው፡ዘይት፡ያዙ። 5፤ሙሽራውም፡በዘገየ፡ጊዜ፡ዅሉ፡እንቅልፍ፡እንቅልፍ፡አላቸውና፡ተኙ። 6፤እኩል፡ሌሊትም፡ሲኾን፦እንሆ፥ሙሽራው፡ይመጣል፥ትቀበሉት፡ዘንድ፡ውጡ፡የሚል፡ውካታ፡ኾነ። 7፤በዚያን፡ጊዜ፡እነዚያ፡ቈነዣዥት፡ዅሉ፡ተነሡና፡መብራታቸውን፡አዘጋጁ። 8፤ሰነፎቹም፡ልባሞቹን፦መብራታችን፡ሊጠፋብን፡ነው፤ከዘይታችኹ፡ስጡን፡አሏቸው። 9፤ልባሞቹ፡ግን፡መልሰው፦ምናልባት፡ለእኛና፡ለእናንተ፡ባይበቃስ፤ይልቅስ፡ወደሚሸጡት፡ኼዳችኹ፡ ለራሳችኹ፡ግዙ፡አሏቸው። 10፤ሊገዙም፡በኼዱ፡ጊዜ፡ሙሽራው፡መጣ፥ተዘጋጅተው፡የነበሩትም፡ከርሱ፡ጋራ፡ወደ፡ሰርግ፡ ገቡ፥ደጁም፡ተዘጋ። 11፤በዃላም፡ደግሞ፡የቀሩቱ፡ቈነዣዥት፡መጡና፦ጌታ፡ሆይ፡ጌታ፡ሆይ፥ክፈትልን፡አሉ። 12፤ርሱ፡ግን፡መልሶ፦እውነት፡እላችዃለኹ፥አላውቃችኹም፡አለ። 13፤ቀኒቱንና፡ሰዓቲቱን፡አታውቁምና፥እንግዲህ፡ንቁ። 14፤ወደ፡ሌላ፡አገር፡የሚኼድ፡ሰው፡ባሮቹን፡ጠርቶ፡ያለውን፡ገንዘብ፡እንደ፡ሰጣቸው፡እንዲሁ፡ይኾናልና፤ 15፤ለያንዳንዱ፡እንደ፡ዐቅሙ፥ለአንዱ፡ዐምስት፡መክሊት፡ለአንዱ፡ኹለት፡ለአንዱም፡አንድ፡ሰጠና፡ወደ፡ ሌላ፡አገር፡ወዲያው፡ኼደ። 16፤ዐምስት፡መክሊትም፡የተቀበለው፡ኼዶ፡ነገደበት፡ሌላም፡ዐምስት፡አተረፈ፤ 17፤እንዲሁም፡ኹለት፡የተቀበለው፡ሌላ፡ኹለት፡አተረፈ። 18፤አንድ፡የተቀበለው፡ግን፡ኼዶ፡ምድርን፡ቈፈረና፡የጌታውን፡ገንዘብ፡ቀበረ። 19፤ከብዙ፡ዘመንም፡በዃላ፡የእነዚያ፡ባሪያዎች፡ጌታ፡መጣና፡ተቈጣጠራቸው። 20፤ዐምስት፡መክሊት፡የተቀበለውም፡ቀረበና፡ሌላ፡ዐምስት፡መክሊት፡አስረክቦ፦ጌታ፡ሆይ፥ዐምስት፡ መክሊት፡ሰጥተኸኝ፡ነበር፤እንሆ፥ሌላ፡ዐምስት፡መክሊት፡አተረፍኹበት፡አለ። 21፤ጌታውም፦መልካም፥አንተ፡በጎ፡ታማኝም፡ባሪያ፤በጥቂቱ፡ታምነኻል፥በብዙ፡እሾምኻለኹ፤ወደ፡ ጌታኽ፡ደስታ፡ግባ፡አለው። 22፤ኹለት፡መክሊትም፡የተቀበለው፡ደግሞ፡ቀርቦ፦ጌታ፡ሆይ፥ኹለት፡መክሊት፡ሰጥተኸኝ፡ ነበር፤እንሆ፥ሌላ፡ኹለት፡መክሊት፡አተረፍኹበት፡አለ። 23፤ጌታውም፦መልካም፥አንተ፡በጎ፥ታማኝም፡ባሪያ፤በጥቂቱ፡ታምነኻል፥በብዙ፡እሾምኻለኹ፥ወደ፡ ጌታኽ፡ደስታ፡ግባ፡አለው። 24፤አንድ፡መክሊትም፡የተቀበለው፡ደግሞ፡ቀርቦ፦ጌታ፡ሆይ፥ካልዘራኽባት፡የምታጭድ፡ካልበተንኽባትም፡ የምትሰበስብ፡ጨካኝ፡ሰው፡መኾንኽን፡ዐውቃለኹ፤ 25፤ፈራኹም፡ኼጄም፡መክሊትኽን፡በምድር፡ቀበርኹት፤እንሆ፥መክሊትኽ፡አለኽ፡አለ። 26፤ጌታውም፡መልሶ፡እንዲህ፡አለው፦አንተ፡ክፉና፡ሀኬተኛ፡ባሪያ፥ካልዘራኹባት፡እንዳጭድ፡ ካልበተንኹባትም፡እንድሰበስብ፡ታውቃለኽን፧ 27፤ስለዚህ፥ገንዘቤን፡ለለዋጮች፡ዐደራ፡ልትሰጠው፡በተገባኽ፡ነበር፥እኔም፡መጥቼ፡ያለኝን፡ከትርፉ፡ጋራ፡ እወስደው፡ነበር። 28፤ስለዚህ፥መክሊቱን፡ውሰዱበት፥ዐሥር፡መክሊትም፡ላለው፡ስጡት፤ 29፤ላለው፡ዅሉ፡ይሰጠዋልና፥ይበዛለትማል፤ከሌለው፡ግን፡ያው፡ያለው፡እንኳ፡ይወሰድበታል። 30፤የማይጠቅመውንም፡ባሪያ፡በውጭ፡ወዳለው፡ጨለማ፡አውጡት፤በዚያ፡ልቅሶና፡ጥርስ፡ማፋጨት፡ ይኾናል። 31፤የሰው፡ልጅ፡በክብሩ፡በሚመጣበት፡ጊዜ፡ከርሱም፡ጋራ፡ቅዱሳን፡መላእክቱ፡ዅሉ፥በዚያን፡ጊዜ፡ በክብሩ፡ዙፋን፡ይቀመጣል፤ 32፤አሕዛብም፡ዅሉ፡በፊቱ፡ይሰበሰባሉ፤እረኛም፡በጎቹን፡ከፍየሎች፡እንደሚለይ፡ርስ፡በርሳቸው፡ይለያቸዋል፥ 33፤በጎችን፡በቀኙ፡ፍየሎችንም፡በግራው፡ያቆማቸዋል። 34፤ንጉሡም፡በቀኙ፡ያሉትን፡እንዲህ፡ይላቸዋል፦እናንተ፡የአባቴ፡ቡሩካን፥ኑ፤ዓለም፡ከተፈጠረበት፡ጊዜ፡ ዠምሮ፡የተዘጋጀላችኹን፡መንግሥት፡ውረሱ። 35፤ተርቤ፡አብልታችኹኛልና፥ተጠምቼ፡አጠጥታችኹኛልና፥እንግዳ፡ኾኜ፡ተቀብላችኹኛልና፥ታርዤ፡ አልብሳችኹኛልና፥ 36፤ታምሜ፡ጠይቃችኹኛልና፥ታስሬ፡ወደ፡እኔ፡መጥታችዃልና። 37፤ጻድቃንም፡መልሰው፡ይሉታል፦ጌታ፡ሆይ፥ተርበኽ፡አይተን፡መቼ፡አበላንኽስ፧ወይስ፡ተጠምተኽ፡ አይተን፡መቼ፡አጠጣንኽ፧ 38፤እንግዳ፡ኾነኽስ፡አይተን፡መቼ፡ተቀበልንኽ፧ወይስ፡ታርዘኽ፡አይተን፡መቼ፡አለበስንኽ፧ 39፤ወይስ፡ታመኽ፡ወይስ፡ታስረኽ፡አይተን፡መቼ፡ወዳንተ፡መጣን፧ 40፤ንጉሡም፡መልሶ፦እውነት፡እላችዃለኹ፥ከዅሉ፡ከሚያንሱ፡ከነዚህ፡ወንድሞቼ፡ለአንዱ፡እንኳ፡ ስላደረጋችኹት፡ለእኔ፡አደረጋችኹት፡ይላቸዋል። 41፤በዚያን፡ጊዜ፡በግራው፡ያሉትን፡ደግሞ፡ይላቸዋል፦እናንተ፡ርጉማን፥ለሰይጣንና፡ለመላእክቱ፡ ወደተዘጋጀ፡ወደዘለዓለም፡እሳት፡ከእኔ፡ኺዱ። 42፤ተርቤ፡አላበላችኹኝምና፥ተጠምቼ፡አላጠጣችኹኝምና፥እንግዳ፡ኾኜ፡አልተቀበላችኹኝምና፥ 43፤ታርዤ፡አላለበሳችኹኝምና፥ታምሜ፡ታስሬም፡አልጠየቃችኹኝምና። 44፤እነርሱ፡ደግሞ፡ይመልሱና፦ጌታ፡ሆይ፥ተርበኽ፡ወይስ፡ተጠምተኽ፡ወይስ፡እንግዳ፡ኾነኽ፡ወይስ፡ ታርዘኽ፡ወይስ፡ታመኽ፡ወይስ፡ታስረኽ፡መቼ፡አይተን፡አላገለገልንኽም፧ይሉታል። 45፤ያን፡ጊዜ፦እውነት፡እላችዃለኹ፥ከዅሉ፡ከሚያንሱ፡ከነዚህ፡ለአንዱ፡ስላላደረጋችኹት፡ለእኔ፡ደግሞ፡ አላደረጋችኹትም፡ብሎ፡ይመልስላቸዋል። 46፤እነዚያም፡ወደዘለዓለም፡ቅጣት፥ጻድቃን፡ግን፡ወደዘለዓለም፡ሕይወት፡ይኼዳሉ።

ምዕራፍ ፳፮

1፤ኢየሱስም፡እነዚህን፡ቃሎች፡ዅሉ፡በፈጸመ፡ጊዜ፥ 2፤ለደቀ፡መዛሙርቱ፦ከኹለት፡ቀን፡በዃላ፡ፋሲካ፡እንዲኾን፡ታውቃላችኹ፥የሰው፡ልጅም፡ሊሰቀል፡ ዐልፎ፡ይሰጣል፡አለ። 3፤በዚያን፡ጊዜ፡የካህናት፡አለቃዎች፡የሕዝብም፡ሽማግሌዎች፡ቀያፋ፡በሚባለው፡በሊቀ፡ካህናቱ፡ግቢ፡ ተሰበሰቡ፥ 4፤ኢየሱስንም፡በተንኰል፡ሊያስይዙት፡ሊገድሉትም፡ተማከሩ፤ 5፤ነገር፡ግን፦በሕዝቡ፡ዘንድ፡ሁከት፡እንዳይነሣ፡በበዓል፡አይኹን፡አሉ። 6፤ኢየሱስም፡በቢታንያ፡በለምጻሙ፡በስምዖን፡ቤት፡ሳለ፥ 7፤አንዲት፡ሴት፡ዋጋው፡እጅግ፡የበዛ፡ሽቱ፡የሞላው፡የአልባስጥሮስ፡ብልቃጥ፡ይዛ፡ወደ፡ርሱ፡ቀረበች፡ በማእዱም፡ተቀምጦ፡ሳለ፡በራሱ፡ላይ፡አፈሰሰችው። 8፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ይህን፡አይተው፡ተቈጡና፦ይህ፡ጥፋት፡ለምንድር፡ነው፧ 9፤ይህ፡በብዙ፡ዋጋ፡ተሽጦ፡ለድኻዎች፡ሊሰጥ፡ይቻል፡ነበርና፥አሉ። 10፤ኢየሱስም፡ይህን፡ዐውቆ፡እንዲህ፡አላቸው፦መልካም፡ሥራ፡ሠርታልኛለችና፡ሴቲቱንስ፡ስለ፡ምን፡ ታደክሟታላችኹ፧ 11፤ድኻዎች፡ዅልጊዜ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ይኖራሉና፥እኔ፡ግን፡ዅልጊዜ፡ከእናንተ፡ጋራ፡አልኖርም፤ 12፤ርሷ፡ይህን፡ሽቱ፡በሰውነቴ፡ላይ፡አፍሳ፟፡ለመቃብሬ፡አደረገች። 13፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ይህ፡ወንጌል፡በዓለም፡ዅሉ፡በማናቸውም፡ስፍራ፡በሚሰበክበት፡ርሷ፡ያደረገችው፡ ደግሞ፡ለርሷ፡መታሰቢያ፡እንዲኾን፡ይነገራል። 14፤በዚያን፡ጊዜ፡የአስቆሮቱ፡ይሁዳ፡የሚባለው፡ከዐሥራ፡ኹለቱ፡አንዱ፡ወደካህናት፡አለቃዎች፡ኼዶ፦ 15፤ምን፡ልትሰጡኝ፡ትወዳላችኹ፡እኔም፡አሳልፌ፡እሰጣችዃለኹ፧እነርሱም፡ሠላሳ፡ብር፡መዘኑለት። 16፤ከዚያችም፡ሰዓት፡ዠምሮ፡አሳልፎ፡ሊሰጠው፡ምቹ፡ጊዜ፡ይሻ፡ነበር። 17፤በቂጣው፡በዓል፡በመዠመሪያ፡ቀን፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ወደ፡ኢየሱስ፡ቀርበው፦ፋሲካን፡ትበላ፡ዘንድ፡ ወዴት፡ልናሰናዳልኽ፡ትወዳለኽ፡አሉት። 18፤ርሱም፦ወደ፡ከተማ፡ከእገሌ፡ዘንድ፡ኼዳችኹ፦መምህር፦ጊዜዬ፡ቀርቧል፤ከደቀ፡መዛሙርቴ፡ጋራ፡ ከአንተ፡ዘንድ፡ፋሲካን፡አደርጋለኹ፡ይላል፡በሉት፡አለ። 19፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ኢየሱስ፡እንዳዘዛቸው፡አደረጉ፡ፋሲካንም፡አሰናዱ። 20፤በመሸም፡ጊዜ፡ከዐሥራ፡ኹለቱ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ጋራ፡በማእዱ፡ተቀመጠ። 21፤ሲበሉም፦እውነት፡እላችዃለኹ፥ከእናንተ፡አንዱ፡እኔን፡አሳልፎ፡ይሰጣል፡አለ። 22፤እጅግም፡አዝነው፡እያንዳንዱ፦ጌታ፡ሆይ፥እኔ፡እኾንን፧ይሉት፡ዠመር። 23፤ርሱም፡መልሶ፦ከእኔ፡ጋራ፡እጁን፡በወጭቱ፡ያጠለቀ፥እኔን፡አሳልፎ፡የሚሰጥ፡ርሱ፡ነው። 24፤የሰው፡ልጅስ፡ስለ፡ርሱ፡እንደ፡ተጻፈ፡ይኼዳል፥ነገር፡ግን፥የሰው፡ልጅ፡ዐልፎ፡ለሚሰጥበት፡ለዚያ፡ ሰው፡ወዮለት፤ያ፡ሰው፡ባልተወለደ፡ይሻለው፡ነበር፡አለ። 25፤አሳልፎ፡የሚሰጠው፡ይሁዳም፡መልሶ፦መምህር፡ሆይ፥እኔ፡እኾንን፧አለ፤አንተ፡አልኽ፡አለው። 26፤ሲበሉም፡ኢየሱስ፡እንጀራን፡አንሥቶ፡ባረከ፡ቈርሶም፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ሰጠና፦እንካችኹ፥ብሉ፡ይህ፡ ሥጋዬ፡ነው፡አለ። 27፤ጽዋንም፡አንሥቶ፡አመስግኖም፡ሰጣቸው፡እንዲህም፡አለ፦ዅላችኹ፡ከርሱ፡ጠጡ፤ 28፤ስለ፡ብዙዎች፡ለኀጢአት፡ይቅርታ፡የሚፈስ፡የዐዲስ፡ኪዳን፡ደሜ፡ይህ፡ነው። 29፤ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥በአባቴ፡መንግሥት፡ከእናንተ፡ጋራ፡ከዚህ፡ከወይን፡ፍሬ፡ዐዲሱን፡ እስከምጠጣበት፡እስከዚያ፡ቀን፡ድረስ፡ከዛሬ፡ዠምሬ፡አልጠጣውም። 30፤መዝሙርም፡ከዘመሩ፡በዃላ፡ወደ፡ደብረ፡ዘይት፡ወጡ። 31፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፦በዚች፡ሌሊት፡ዅላችኹ፡በእኔ፡ትሰናከላላችኹ፤እረኛውን፡እመታለኹ፡ የመንጋውም፡በጎች፡ይበተናሉ፡የሚል፡ተጽፏልና፤ 32፤ከተነሣኹ፡በዃላ፡ግን፡ወደ፡ገሊላ፡እቀድማችዃለኹ፡አላቸው። 33፤ጴጥሮስም፡መልሶ፦ዅሉም፡ባንተ፡ቢሰናከሉ፡እኔ፡ከቶ፡አልሰናከልም፡አለው። 34፤ኢየሱስ፦እውነት፡እልኻለኹ፥በዚች፡ሌሊት፡ዶሮ፡ሳይጮኽ፡ሦስት፡ጊዜ፡ትክደኛለኽ፡አለው። 35፤ጴጥሮስ፦ከአንተ፡ጋራ፡መሞት፡እንኳ፡የሚያስፈልገኝ፡ቢኾን፥ከቶ፡አልክድኽም፡አለው።ደቀ፡ መዛሙርቱ፡ዅሉ፡ደግሞ፡እንደዚሁ፡አሉ። 36፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡ከነርሱ፡ጋራ፡ጌቴሴማኒ፡ወደምትባል፡ስፍራ፡መጣ፡ደቀ፡መዛሙርቱንም፦ወዲያ፡ ኼጄ፡ስጸልይ፡ሳለ፡በዚህ፡ተቀመጡ፡አላቸው። 37፤ጴጥሮስንም፡ኹለቱንም፡የዘብዴዎስን፡ልጆች፡ወስዶ፡ሊያዝን፡ሊተክዝም፡ዠመር። 38፤ነፍሴ፡እስከ፡ሞት፡ድረስ፡እጅግ፡ዐዘነች፤በዚህ፡ቈዩ፥ከእኔም፡ጋራ፡ትጉ፡አላቸው። 39፤ጥቂትም፡ወደ፡ፊት፡እልፍ፡ብሎ፡በፊቱ፡ወደቀና፡ሲጸልይ፦አባቴ፥ቢቻልስ፥ይህች፡ጽዋ፡ከእኔ፡ ትለፍ፤ነገር፡ግን፥አንተ፡እንደምትወድ፡ይኹን፡እንጂ፡እኔ፡እንደምወድ፡አይኹን፡አለ። 40፤ወደ፡ደቀ፡መዛሙርቱም፡መጣ፤ተኝተውም፡አገኛቸውና፡ጴጥሮስን፦እንዲሁም፡ከእኔ፡ጋራ፡አንዲት፡ ሰዓት፡እንኳ፡ልትተጉ፡አልቻላችኹምን፧ 41፤ወደ፡ፈተና፡እንዳትገቡ፡ትጉና፡ጸልዩ፤መንፈስስ፡ተዘጋጅታለች፡ሥጋ፡ግን፡ደካማ፡ነው፡አለው። 42፤ደግሞ፡ኹለተኛ፡ኼዶ፡ጸለየና፦አባቴ፥ይህች፡ጽዋ፡ሳልጠጣት፡ታልፍ፡ዘንድ፡የማይቻል፡እንደ፡ ኾነ፥ፈቃድኽ፡ትኹን፡አለ። 43፤ደግሞም፡መጥቶ፡ዐይኖቻቸው፡በእንቅልፍ፡ከብደው፡ነበርና፥ተኝተው፡አገኛቸው። 44፤ደግሞም፡ትቷቸው፡ኼደ፥ሦስተኛም፡ያንኑ፡ቃል፡ደግሞ፡ጸለየ። 45፤ከዚያ፡ወዲያ፡ወደ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡መጥቶ፦እንግዲህስ፡ተኙ፡ዕረፉም፤እንሆ፥ሰዓቲቱ፡ቀርባለች፡ የሰው፡ልጅም፡በኀጢአተኛዎች፡እጅ፡ዐልፎ፡ይሰጣል። 46፤ተነሡ፥እንኺድ፤እንሆ፥አሳልፎ፡የሚሰጠኝ፡ቀርቧል፡አላቸው። 47፤ይህንም፡ገና፡ሲናገር፥እንሆ፥ከዐሥራ፡ኹለቱ፡አንዱ፡ይሁዳ፡መጣ፥ከርሱም፡ጋራ፡ብዙ፡ሕዝብ፡ ሰይፍና፡ጐመድ፡ይዘው፡ከካህናት፡አለቃዎችና፡ከሕዝቡ፡ሽማግሌዎች፡ዘንድ፡መጡ። 48፤አሳልፎ፡የሚሰጠውም፦የምስመው፡ርሱ፡ነው፤ያዙት፡ብሎ፡ምልክት፡ሰጥቷቸው፡ነበር። 49፤ወዲያውም፡ወደ፡ኢየሱስ፡ቀረበና፦መምህር፡ሆይ፥ሰላም፡ለአንተ፡ይኹን፡ብሎ፡ሳመው። 50፤ኢየሱስም፦ወዳጄ፡ሆይ፥ለምን፡ነገር፡መጣኽ፧አለው።በዚያን፡ጊዜ፡ቀረቡ፡እጃቸውንም፡በኢየሱስ፡ ላይ፡ጭነው፡ያዙት። 51፤እንሆም፥ከኢየሱስ፡ጋራ፡ከነበሩት፡አንዱ፡እጁን፡ዘርግቶ፡ሰይፉን፡መዘዘና፡የሊቀ፡ካህናቱን፡ባሪያ፡መቶ፟፡ ዦሮውን፡ቈረጠው። 52፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡እንዲህ፡አለው፦ሰይፍ፡የሚያነሡ፡ዅሉ፡በሰይፍ፡ይጠፋሉና፡ሰይፍኽን፡ወደ፡ ስፍራው፡መልስ። 53፤ወይስ፡አባቴን፡እንድለምን፡ርሱም፡አኹን፡ከዐሥራ፡ኹለት፡ጭፍራዎች፡የሚበዙ፡መላእክት፡ እንዲሰድልኝ፡የማይቻል፡ይመስልኻልን፧ 54፤እንዲህ፡ከኾነስ፦እንደዚህ፡ሊኾን፡ይገ፟ባ፟ል፡የሚሉ፡መጻሕፍት፡እንዴት፡ይፈጸማሉ፧ 55፤በዚያን፡ሰዓት፡ኢየሱስ፡ለሕዝቡ፦ወንበዴን፡እንደምትይዙ፡ሰይፍና፡ጐመድ፡ይዛችኹ፡ልትይዙኝ፡ ወጣችኹን፧በመቅደስ፡ዕለት፡ዕለት፡እያስተማርኹ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ስቀመጥ፡ሳለኹ፡አልያዛችኹኝም። 56፤ነገር፡ግን፥ይህ፡ዅሉ፡የኾነ፡የነቢያት፡መጻሕፍት፡ይፈጸሙ፡ዘንድ፡ነው፡አለ።በዚያን፡ጊዜ፡ደቀ፡ መዛሙርቱ፡ዅሉ፡ትተውት፡ሸሹ። 57፤ኢየሱስን፡የያዙትም፡ጻፊዎችና፡ሽማግሌዎች፡ወደተከማቹበት፡ወደ፡ሊቀ፡ካህናቱ፡ወደ፡ቀያፋ፡ወሰዱት። 58፤ጴጥሮስ፡ግን፡እስከሊቀ፡ካህናቱ፡ግቢ፡ድረስ፡ሩቅ፡ኾኖ፡ተከተለው፥የነገሩንም፡ፍጻሜ፡ያይ፡ዘንድ፡ ወደ፡ውስጥ፡ገብቶ፡ከሎሌዎቹ፡ጋራ፡ተቀመጠ። 59፤የካህናት፡አለቃዎችና፡ሽማግሌዎች፡ሸንጎውም፡ዅሉ፡እንዲገድሉት፡በኢየሱስ፡ላይ፡የሐሰት፡ምስክር፡ ይፈልጉ፡ነበር፥አላገኙም፤ 60፤ብዙም፡የሐሰት፡ምስክሮች፡ምንም፡ቢቀርቡ፡አላገኙም። 61፤በዃላም፡ኹለት፡ቀርበው፦ይህ፡ሰው፦የእግዚአብሔርን፡ቤተ፡መቅደስ፡አፍርሼ፡በሦስት፡ቀን፡ ልሠራው፡እችላለኹ፡ብሏል፡አሉ። 62፤ሊቀ፡ካህናቱም፡ተነሥቶ፦እነዚህ፡ለሚመሰክሩብኽ፡አንድ፡ስንኳ፡አትመልስምን፧አለው። 63፤ኢየሱስ፡ግን፡ዝም፡አለ።ሊቀ፡ካህናቱም፦አንተ፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ክርስቶስ፡የኾንኽ፡እንደ፡ኾነ፡ እንድትነግረን፡በሕያው፡እግዚአብሔር፡አምልኻለኹ፡አለው። 64፤ኢየሱስም፦አንተ፡አልኽ፥ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥ከእንግዲህ፡ወዲህ፡የሰው፡ልጅ፡በኀይል፡ቀኝ፡ ሲቀመጥ፥በሰማይም፡ደመና፡ሲመጣ፡ታያላችኹ፡አለው። 65፤በዚያን፡ጊዜ፡ሊቀ፡ካህናቱ፡ልብሱን፡ቀዶ፦ተሳድቧል፡እንግዲህ፡ወዲህ፡ምስክሮች፡ስለ፡ምን፡ ያስፈልገናል፧እንሆ፥ስድቡን፡አኹን፡ሰምታችዃል፤ምን፡ይመስላችዃል፧አለ። 66፤እነርሱም፦ሞት፡ይገ፟ባ፟ዋል፡ብለው፡መለሱ። 67፤በዚያን፡ጊዜ፡በፊቱ፡ተፉበት፤ጐሰሙትም፥ሌላዎችም፡በጥፊ፡መትተው፦ክርስቶስ፡ሆይ፥በጥፊ፡ የመታኽ፡ማን፡ነው፧ 68፤ትንቢት፡ተናገርልን፡አሉ። 69፤ጴጥሮስም፡ከቤት፡ውጭ፡በዐጥሩ፡ግቢ፡ተቀምጦ፡ነበር፤አንዲት፡ገረድም፡ወደ፡ርሱ፡ቀርባ፦አንተ፡ ደግሞ፡ከገሊላው፡ከኢየሱስ፡ጋራ፡ነበርኽ፡አለችው። 70፤ርሱ፡ግን፦የምትዪውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡በዅሉ፡ፊት፡ካደ። 71፤ወደ፡በሩም፡ሲወጣ፡ሌላዪቱ፡አየችውና፡በዚያ፡ላሉት፦ይህ፡ደግሞ፡ከናዝሬቱ፡ከኢየሱስ፡ጋራ፡ነበረ፡ አለች። 72፤ዳግመኛም፡ሲምል።ሰውየውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡ካደ። 73፤ጥቂትም፡ቈይተው፡በዚያ፡ቆመው፡የነበሩ፡ቀርበው፡ጴጥሮስን፦አነጋገርኽ፡ይገልጥኻልና፥በእውነት፡ አንተ፡ደግሞ፡ከነርሱ፡ወገን፡ነኽ፡አሉት። 74፤በዚያን፡ጊዜ፦ሰውየውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡ሊራገምና፡ሊምል፡ዠመረ።ወዲያውም፡ዶሮ፡ጮኸ። 75፤ጴጥሮስም፦ዶሮ፡ሳይጮኽ፡ሦስት፡ጊዜ፡ትክደኛለኽ፡ያለው፡የኢየሱስ፡ቃል፡ትዝ፡አለው፤ወደ፡ ውጭም፡ወጥቶ፡መራራ፡ልቅሶ፡አለቀሰ።

ምዕራፍ ፳፯

1፤ሲነጋም፡የካህናት፡አለቃዎችና፡የሕዝቡ፡ሽማግሌዎች፡ዅሉ፡ሊገድሉት፡በኢየሱስ፡ላይ፡ተማከሩ፤ 2፤አስረውም፡ወሰዱት፥ለገዢው፡ለጰንጤናዊው፡ጲላጦስም፡አሳልፈው፡ሰጡት። 3፤በዚያን፡ጊዜ፡አሳልፎ፡የሰጠው፡ይሁዳ፡እንደ፡ተፈረደበት፡አይቶ፡ተጸጸተ፥ሠላሳውንም፡ብር፡ለካህናት፡ አለቃዎችና፡ለሽማግሌዎች፡መልሶ፦ 4፤ንጹሕ፡ደም፡አሳልፌ፡በመስጠቴ፡በድያለኹ፡አለ።እነርሱ፡ግን፦እኛስ፡ምን፡አግዶን፧አንተው፡ ተጠንቀቅ፡አሉ። 5፤ብሩንም፡በቤተ፡መቅደስ፡ጥሎ፡ኼደና፡ታንቆ፡ሞተ። 6፤የካህናት፡አለቃዎችም፡ብሩን፡አንሥተው፦የደም፡ዋጋ፡ነውና፥ወደ፡መባ፡ልንጨምረው፡አልተፈቀደም፡ አሉ። 7፤ተማክረውም፡የሸክላ፡ሠሪውን፡መሬት፡ለእንግዳዎች፡መቃብር፡ገዙበት። 8፤ስለዚህ፥ያ፡መሬት፡እስከ፡ዛሬ፡ድረስ፡የደም፡መሬት፡ተባለ። 9፤በዚያን፡ጊዜ፡በነቢዩ፡በኤርምያስ፡የተባለው፦ከእስራኤል፡ልጆችም፡አንዳንዶቹ፡የገመቱትን፥የተገመተውን፡ ዋጋ፡ሠላሳ፡ብር፡ያዙ፥ 10፤ጌታም፡እንዳዘዘኝ፡ስለሸክላ፡ሠሪ፡መሬት፡ሰጡት።የሚል፡ተፈጸመ። 11፤ኢየሱስም፡በገዢው፡ፊት፡ቆመ፤ገዢውም፦የአይሁድ፡ንጉሥ፡አንተ፡ነኽን፧ብሎ፡ ጠየቀው፤ኢየሱስም፦አንተ፡አልኽ፡አለው። 12፤የካህናት፡አለቃዎችም፡ሽማግሌዎችም፡ሲከሱት፡ምንም፡አልመለሰም። 13፤በዚያን፡ጊዜ፡ጲላጦስ፦ስንት፡ያኽል፡እንዲመሰክሩብኽ፡አትሰማምን፧አለው። 14፤ገዢውም፡እጅግ፡እስኪደነቅ፡ድረስ፡አንዲት፡ቃል፡ስንኳ፡አልመለሰለትም። 15፤በዚያም፡በዓል፡ሕዝቡ፡የወደዱትን፡አንድ፡እስረኛ፡ሊፈታላቸው፡ለገዢው፡ልማድ፡ነበረው። 16፤በዚያን፡ጊዜም፡በርባን፡የሚባል፡በጣም፡የታወቀ፡እስረኛ፡ነበራቸው። 17፤እንግዲህ፡እነርሱ፡ተሰብስበው፡ሳሉ፡ጲላጦስ፦በርባንን፡ወይስ፡ክርስቶስ፡የተባለውን፡ኢየሱስን፡ ማንኛውን፡ልፈታላችኹ፡ትወዳላችኹ፧አላቸው፤ 18፤በቅንአት፡አሳልፈው፡እንደ፡ሰጡት፡ያውቅ፡ነበርና። 19፤ርሱም፡በፍርድ፡ወንበር፡ተቀምጦ፡ሳለ፥ሚስቱ፦ስለ፡ርሱ፡ዛሬ፡በሕልም፡እጅግ፡መከራ፡ ተቀብያለኹና፥በዚያ፡ጻድቅ፡ሰው፡ምንም፡አታድርግ፡ብላ፡ላከችበት። 20፤የካህናት፡አለቃዎችና፡ሽማግሌዎች፡ግን፡በርባንን፡እንዲለምኑ፡ኢየሱስን፡ግን፡እንዲያጠፉ፡ሕዝቡን፡ አባበሉ። 21፤ገዢውም፡መልሶ፦ከኹለቱ፡ማንኛውን፡ልፈታላችኹ፡ትወዳላችኹ፧አላቸው፤እነርሱም፦በርባንን፡አሉ። 22፤ጲላጦስ፦ክርስቶስ፡የተባለውን፡ኢየሱስን፡እንግዲህ፡ምን፡ላድርገው፧አላቸው፤ዅሉም፦ይሰቀል፡አሉ። 23፤ገዢውም፦ምን፡ነው፧ያደረገው፡ክፋት፡ምንድር፡ነው፧አለ፤እነርሱ፡ግን፦ይሰቀል፡እያሉ፡ጩኸት፡ አበዙ። 24፤ጲላጦስም፡ሁከት፡እንዲዠመር፡እንጂ፡አንዳች፡እንዳይረባ፡ባየ፡ጊዜ፥ውሃ፡አንሥቶ፦እኔ፡ከዚህ፡ ጻድቅ፡ሰው፡ደም፡ንጹሕ፡ነኝ፤እናንተ፡ተጠንቀቁ፡ሲል፡በሕዝቡ፡ፊት፡እጁን፡ታጠበ። 25፤ሕዝቡም፡ዅሉ፡መልሰው፦ደሙ፡በእኛና፡በልጆቻችን፡ላይ፡ይኹን፡አሉ። 26፤በዚያን፡ጊዜ፡በርባንን፡ፈታላቸው፥ኢየሱስን፡ግን፡ገርፎ፡ሊሰቀል፡አሳልፎ፡ሰጠ። 27፤በዚያን፡ጊዜ፡የገዢው፡ወታደሮች፡ኢየሱስን፡ወደገዢው፡ግቢ፡ውስጥ፡ወሰዱት፡ጭፍራውንም፡ዅሉ፡ ወደ፡ርሱ፡አከማቹ። 28፤ልብሱንም፡ገፈው፡ቀይ፡ልብስ፡አለበሱት፥ 29፤ከሾኽም፡አክሊል፡ጐንጉነው፡በራሱ፡ላይ፥በቀኝ፡እጁም፡መቃ፡አኖሩ፥በፊቱም፡ተንበርክከው፦የአይሁድ፡ንጉሥ፡ሆይ፥ሰላም፡ለአንተ፡ይኹን፡እያሉ፡ዘበቱበት፤ 30፤ተፉበትም፡መቃውንም፡ይዘው፡ራሱን፡መቱት። 31፤ከዘበቱበትም፡በዃላ፡ቀዩን፡ልብስ፡ገፈፉት፥ልብሱንም፡አለበሱት፡ሊሰቅሉትም፡ወሰዱት። 32፤ሲወጡም፡ስምዖን፡የተባለው፡የቀሬናን፡ሰው፡አገኙ፤ርሱንም፡መስቀሉን፡ይሸከም፡ዘንድ፡አስገደዱት። 33፤ትርጓሜው፡የራስ፡ቅል፡ስፍራ፡ወደሚኾን፥ጎልጎታ፡ወደሚባለው፡ስፍራ፡በደረሱ፡ጊዜም፥ 34፤በሐሞት፡የተደባለቀ፡የወይን፡ጠጅ፡ሊጠጣ፡አቀረቡለት፤ቀምሶም፡ሊጠጣው፡አልወደደም። 35፤ከሰቀሉትም፡በዃላ፡ልብሱን፡ዕጣ፡ጥለው፡ተካፈሉ፥ 36፤በዚያም፡ተቀምጠው፡ይጠብቁት፡ነበር። 37፤ይህ፡ኢየሱስ፡የአይሁድ፡ንጉሥ፡ነው፡የሚል፡የክሱን፡ጽሕፈት፡ከራሱ፡በላይ፡አኖሩ። 38፤በዚያን፡ጊዜ፡ኹለት፡ወንበዴዎች፡አንዱ፡በቀኝ፡አንዱም፡በግራ፡ከርሱ፡ጋራ፡ተሰቀሉ። 39፤የሚያልፉትም፡ራሳቸውን፡እየነቀነቁ፡ይሰድቡት፡ነበርና። 40፤ቤተ፡መቅደስን፡የምታፈርስ፡በሦስት፡ቀንም፡የምትሠራው፥ራስኽን፡አድን፤የእግዚአብሔር፡ልጅስ፡ ከኾንኽ፡ከመስቀል፡ውረድ፡አሉት። 41፤እንዲሁም፡ደግሞ፡የካህናት፡አለቃዎች፡ከጻፊዎችና፡ከሽማግሌዎች፡ጋራ፡እየዘበቱበት፡እንዲህ፡አሉ። 42፤ሌላዎችን፡አዳነ፥ራሱን፡ሊያድን፡አይችልም፤የእስራኤል፡ንጉሥ፡ከኾነ፥አኹን፡ከመስቀል፡ይውረድ፡ እኛም፡እናምንበታለን። 43፤በእግዚአብሔር፡ታምኗል፤የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ነኝ፡ብሏልና፥ከወደደውስ፡አኹን፡ያድነው። 44፤ከርሱ፡ጋራ፡የተሰቀሉት፡ወንበዴዎች፡ደግሞ፡ያንኑ፡እያሉ፡ይነቅፉት፡ነበር። 45፤ከስድስት፡ሰዓትም፡ዠምሮ፡እስከ፡ዘጠኝ፡ሰዓት፡ድረስ፡በምድር፡ዅሉ፡ላይ፡ጨለማ፡ኾነ። 46፤በዘጠኝ፡ሰዓትም፡ኢየሱስ፦ኤሎሄ፥ኤሎሄ፥ላማ፡ሰበቅታኒ፧ብሎ፡በታላቅ፡ድምፅ፡ ጮኸ።ይህም፦አምላኬ፡አምላኬ፥ስለ፡ምን፡ተውኸኝ፧ማለት፡ነው። 47፤በዚያም፡ከቆሙት፡ሰዎች፡ሰምተው፦ይህስ፡ኤልያስን፡ይጠራል፡አሉ። 48፤ወዲያውም፡ከነርሱ፡አንዱ፡ሮጠ፤ሰፍነግም፡ይዞ፡ሖምጣጤ፡ሞላበት፥በመቃም፡አድርጎ፡አጠጣው። 49፤ሌላዎቹ፡ግን፦ተው፥ኤልያስ፡መጥቶ፡ያድነው፡እንደ፡ኾነ፡እንይ፡አሉ። 50፤ኢየሱስም፡ኹለተኛ፡በታላቅ፡ድምፅ፡ጮኾ፡ነፍሱን፡ተወ። 51፤እንሆም፥የቤተ፡መቅደስ፡መጋረጃ፡ከላይ፡እስከ፡ታች፡ከኹለት፡ተቀደደ፥ምድርም፡ ተናወጠች፥አለቶችም፡ተሰነጠቁ፤ 52፤መቃብሮችም፡ተከፈቱ፥ተኝተው፡ከነበሩትም፡ከቅዱሳን፡ብዙ፡ሥጋዎች፡ተነሡ፤ 53፤ከትንሣኤውም፡በዃላ፡ከመቃብሮች፡ወጥተው፡ወደ፡ቅድስት፡ከተማ፡ገቡና፡ለብዙዎች፡ታዩ። 54፤የመቶ፡አለቃም፡ከርሱም፡ጋራ፡ኢየሱስን፡የሚጠብቁ፡መናወጡንና፡የኾነውን፡ነገር፡አይተው፦ይህ፡ በእውነት፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ነበረ፡ብለው፡እጅግ፡ፈሩ። 55፤ኢየሱስን፡እያገለገሉ፡ከገሊላ፡የተከተሉት፡ብዙ፡ሴቶች፡በሩቅ፡ኾነው፡ሲመለከቱ፡በዚያ፡ነበሩ፤ 56፤ከነርሱም፡መግደላዊት፡ማርያምና፡የያዕቆብና፡የዮሳ፡እናት፡ማርያም፡የዘብዴዎስም፡የልጆቹ፡እናት፡ነበሩ። 57፤በመሸም፡ጊዜ፡ዮሴፍ፡የተባለው፡ባለጠጋ፡ሰው፡ከአርማትያስ277፡መጣ፥ርሱም፡ደግሞ፡የኢየሱስ፡ደቀ፡ 277 ዕብ.፥ራማህ። መዝሙር፡ነበረ፤ 58፤ይኸውም፡ወደ፡ጲላጦስ፡ቀርቦ፡የኢየሱስን፡ሥጋ፡ለመነው። 59፤ጲላጦስም፡እንዲሰጡት፡አዘዘ።ዮሴፍም፡ሥጋውን፡ይዞ፡በንጹሕ፡በፍታ፡ከፈነው፥ 60፤ከአለት፡በወቀረው፡በዐዲሱ፡መቃብርም፡አኖረው፥በመቃብሩም፡ደጃፍ፡ታላቅ፡ድንጋይ፡አንከባሎ፡ኼደ። 61፤መግደላዊት፡ማርያምም፡ኹለተኛዪቱም፡ማርያም፡በመቃብሩ፡አንጻር፡ተቀምጠው፡በዚያ፡ነበሩ። 62፤በማግስቱም፡ከመዘጋጀት፡በዃላ፡በሚኾነው፡ቀን፥የካህናት፡አለቃዎችና፡ፈሪሳውያን፡ወደ፡ጲላጦስ፡ ተሰበሰቡና፦ 63፤ጌታ፡ሆይ፥ያ፡አሳች፡በሕይወቱ፡ገና፡ሳለ፦ከሦስት፡ቀን፡በዃላ፡እነሣለኹ፡እንዳለ፡ትዝ፡አለን። 64፤እንግዲህ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡መጥተው፡በሌሊት፡እንዳይሰርቁት፡ለሕዝቡም፦ከሙታን፡ተነሣ፡እንዳይሉ፥የዃለኛዪቱ፡ስሕተት፡ከፊተኛዪቱ፡ይልቅ፡የከፋች፡ትኾናለችና፡መቃብሩ፡እስከ፡ሦስተኛ፡ቀን፡ ድረስ፡እንዲጠበቅ፡እዘዝ፡አሉት። 65፤ጲላጦስም፦ጠባቂዎች፡አሏችኹ፤ኼዳችኹ፡እንዳወቃችኹ፡አስጠብቁ፡አላቸው። 66፤እነርሱም፡ኼደው፡ከጠባቂዎች፡ጋራ፡ድንጋዩን፡ዐትመው፡መቃብሩን፡አስጠበቁ።

ምዕራፍ ፳፰

1፤በሰንበትም፡መጨረሻ፡መዠመሪያው፡ቀን፡ሲነጋ፡መግደላዊት፡ማርያምና፡ኹለተኛዪቱ፡ማርያም፡ መቃብሩን፡ሊያዩ፡መጡ። 2፤እንሆም፥የጌታ፡መልአክ፡ከሰማይ፡ስለ፡ወረደ፡ታላቅ፡የምድር፡መናወጥ፡ኾነ፤ቀርቦም፡ድንጋዩን፡ አንከባሎ፡በላዩ፡ተቀመጠ። 3፤መልኩም፡እንደ፡መብረቅ፡ልብሱም፡እንደ፡በረዶ፡ነጭ፡ነበረ። 4፤ጠባቂዎቹም፡ርሱን፡ከመፍራት፡የተነሣ፡ተናወጡ፡እንደ፡ሞቱም፡ኾኑ። 5፤መልአኩም፡መልሶ፡ሴቶቹን፡አላቸው፦እናንተስ፡አትፍሩ፥የተሰቀለውን፡ኢየሱስን፡እንድትሹ፡ ዐውቃለኹና፤ 6፤እንደ፡ተናገረ፡ተነሥቷልና፥በዚህ፡የለም፤የተኛበትን፡ስፍራ፡ኑና፡እዩ። 7፤ፈጥናችኹም፡ኺዱና፦ከሙታን፡ተነሣ፥እንሆም፥ወደ፡ገሊላ፡ይቀድማችዃል፡በዚያም፡ታዩታላችኹ፡ ብላችኹ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ንገሯቸው።እንሆም፥ነገርዃችኹ። 8፤በፍርሀትና፡በታላቅ፡ደስታም፡ፈጥነው፡ከመቃብር፡ኼዱ፥ለደቀ፡መዛሙርቱም፡ሊያወሩ፡ሮጡ። 9፤እንሆም፥ኢየሱስ፡አገኛቸውና፦ደስ፡ይበላችኹ፡አላቸው።እነርሱም፡ቀርበው፡እግሩን፡ይዘው፡ሰገዱለት። 10፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፦አትፍሩ፤ኼዳችኹ፡ወደ፡ገሊላ፡እንዲኼዱ፡ለወንድሞቼ፡ተናገሩ፥በዚያም፡ ያዩኛል፡አላቸው። 11፤ሲኼዱም፡ሳሉ፥እንሆ፥ከጠባቂዎቹ፡አንዳንድ፡ወደ፡ከተማ፡መጥተው፡የኾነውን፡ዅሉ፡ለካህናት፡ አለቃዎች፡አወሩ። 12፤ከሽማግሌዎች፡ጋራም፡ተሰብስበው፡ተማከሩና፡ለጭፍራዎች፡ብዙ፡ገንዘብ፡ሰጥተዋቸው። 13፤እኛ፡ተኝተን፡ሳለን፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡በሌሊት፡መጥተው፡ሰረቁት፡በሉ። 14፤ይህም፡በገዢው፡ዘንድ፡የተሰማ፡እንደ፡ኾነ፥እኛ፡እናስረዳዋለን፡እናንተም፡ያለሥጋት፡እንድትኾኑ፡ እናደርጋለን፡አሏቸው። 15፤እነርሱም፡ገንዘቡን፡ተቀብለው፡እንዳስተማሯቸው፡አደረጉ።ይህም፡ነገር፡በአይሁድ፡ዘንድ፡እስከ፡ዛሬ፡ ድረስ፡ሲወራ፡ይኖራል። 16፤ዐሥራ፡አንዱ፡ደቀ፡መዛሙርት፡ግን፡ኢየሱስ፡ወዳዘዛቸው፡ተራራ፡ወደ፡ገሊላ፡ኼዱ፥ 17፤ባዩትም፡ጊዜ፡ሰገዱለት፤የተጠራጠሩ፡ግን፡ነበሩ። 18፤ኢየሱስም፡ቀረበና፡እንዲህ፡ብሎ፡ተናገራቸው፦ሥልጣን፡ዅሉ፡በሰማይና፡በምድር፡ተሰጠኝ። 19-20፤እንግዲህ፡ኺዱና፡አሕዛብን፡ዅሉ፡በአብ፡በወልድና፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡ስም፡ እያጠመቃችዃቸው፥ያዘዝዃችኹንም፡ዅሉ፡እንዲጠብቁ፡እያስተማራችዃቸው፡ደቀ፡መዛሙርት፡ አድርጓቸው፤እንሆም፡እኔ፡እስከ፡ዓለም፡ፍጻሜ፡ድረስ፡ዅልጊዜ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ነኝ፨









: