ከ«ደብረ ዳሞ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
No edit summary Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
No edit summary Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit |
||
መስመር፡ 1፦ | መስመር፡ 1፦ | ||
{{አለት ፍልፍል |
{{አለት ፍልፍል |
||
|ስም = ደብረ ዳሞ |
|ስም = '''ደብረ ዳሞ''' |
||
|infoboxwidth= 22.8em |
|infoboxwidth= 22.8em |
||
|ስዕል = Debre Damo Church.jpg |
|ስዕል = Debre Damo Church.jpg |
እትም በ09:58, 26 ኦክቶበር 2019
| ||||
---|---|---|---|---|
ደብረ ዳሞ | ||||
ደብረ ዳሞ ገዳም በጥንታዊ የህንጻ አሰራር ዘዴ | ||||
አገር | ኢትዮጵያ | |||
ሌላ ስም | {{{ሌላ ስም}}} | |||
ዓይነት | አራት መዐዘን | |||
አካባቢ** | አዲግራት ፣ ትግራይ | |||
የቅርስነት ታሪክ | ||||
ቅርሱ የተሰራበት ዘመን | ፮ኛው ክፍለዘመን | |||
* የአለበት ቦታ ** የዩ.ኔ.ስ.ኮ. ክልል ክፍፍል |
ደብረ ዳሞ በ6ኛው ክፍለ ዘመን የተቆረቆረ ገዳምና ይህ ገዳም የሚኖርበት ተራራ ስም ነው። ደብረ ዳሞ ከአዲግራት በስተምዕራብ በመካከለኛው ትግራይ ይገኛል። ከተራራው ቀጥ ብሎ ለመውጣት አዳጋችነቱ የተነሳ ወደገዳሙ ለመድረስ ከቆዳ በተሰራ ገምድ ላይ መንጠላጠል ግድ ይላል። ቤተ ክርስቲያኑ በኢትዮጵያ ውስጥ ጥንታዊ የአሰራር ዘዴን ተከተሎ እስካሁን ዘመን ድረስ በመዝለቅ ቀደምትነት ስፍራን ይይዛል ።
የተሰራውም በአቡነ አረጋዊ በ6ኛው ክፍለ ዘመን እንደነበር ትውፊት አለ። ቶማስ ፓከናም የተባለው የታሪክ ተመራማሪ አምባው እንደ ወህኒና አምባ ግሸን ወንድ የነገስታት ዝርያወችን ለማሰሪያነት ያገለግል እንደነበር ትውፊት እንዳለ በጥናት ደርሶበታል። [1] የገዳሙ ውጫዊ ወለሎች በጥንቱ ዘመን ዘዴ፣ የኖራ ድንጋይንና የጥድ እንጨትን በማፈራረቅ የተሰራ ነበር። ይህም በስነ ህንጻ ጥበበ አክሱማዊ ዘዴ አሰራር ይባላል።[2]
እዚህ አምባ ላይ የሰውም ሆነ የእንስሳ ሴቶች መውጣት አጥብቆ የተከለከለ ነው። ሆኖም ግን በግራኝ አህመድ ወረራ ወቅት ንግስት ሰብለ ወንጌል እና ደንገጡሮቻ እዚህ አምባ ላይ በመጠለል ከሞት ድነዋል። ተራራው ላይ ምንጭና እህል የሚዘራበት ሰፊ መሬት ስለነበር ፖርቱጋሎቹ እነ ክሪስታቮ ደጋማ ከአምባው ደርሰው ንግስቲቱ እንድትወርድ እስከአሳመኗት ድረስ የግራኝን ሰራዊት ከዚህ አምባ ላይ ሆና መከላከል ችላለች።
-
ደብረ ዳሞ አምባ ከሩቁ - ምኩራቡ በሁሉም አቅጣጫ አንድ አይነት ኩርባ ያለው የተፈጥሮ ቅጥር ነው
-
ደብረ ዳሞ መወጣጫ ጠፍር
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |